qበካፋ ዞን ሳይለም ወረዳ ከ78 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ግንባታቸው የተጠናቀቁ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተመረቁ ።we

Spread the love

የያዶታ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅና የያዶታ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ቀዶ ጥገና ማዕከል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል።

ኮሌጁ በ 66 ነጥብ 9 ሚለዮን ብር አዲስ ባስገነባው ህንጻ የአስተዳደር ክፍል፣የተማሪዎች መማሪያ ክፍሎች እና ቤተመጻሕፍት ክፍል የተካተተበት መሆኑ ታውቋል።

በሌላ በኩልም በክልሉ መንግስት ከ 11 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባ የያዶታ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ የቀዶ ጥገና ማዕከል ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል ።

በምረቃው ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ፣ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃፊ አቶ ማስረሻ በላቸዉን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና የካፋ ዞን አመራሮች እንዲሁም የያዶታ ከተማ ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

በታጠቅ አበበ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *