




በክልል፣ በዞንና፣ በወረዳ በከተማ አስተዳደር የሚገኙ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን አመራሮችና ባለሙያዎች በዳውሮ ዞን ታርጫ ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎችን ጉበኙ።
የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ተቋማት አመራሮችና ባለሙያዎች በከተማ አስተዳደሩ በተደራጁ ወጣቶች እየተሰራ የሚገኝ የዶሮ እርባታ ማዕከል፣ የከተማ ግብርና ስራዎችንና የከተማ ኮሪደር ልማት ስራዎችን ተዟዙረው ጎብኝተዋል
በጉብኝቱ የተገኙ የደቡብ ምዕራብ ሚዲያ ኔትወርክ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ መንግስቱ መኩሪያ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ በመንግስትና ህብረተሰብ ተሳትፎ የሚከናወኑ ተግባራት ለማስተዋወቅ ያላቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑን አስረድተዋል።
ተቋማቱ ጠንካራ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ተግባር በማከናወን በአገር ግንባታ ላይ ያላቸውን ሚና መወጣት ልወጡ ይገባልም ብለዋል።
መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረገ መሆኑን የገለፁ የተደራጁ ወጣቶች በተለይ ስራ አጣን የሚሉ ዜጎች የስራ ባህልንና አመለካከትን በመቀየር በየትኛውም የስራ ዘርፍ በመሰማራት ውጤታማ መሆን እንደሚቻል አስረድተዋል።
በከተማ አስተዳደሩ እየተሰሩ ያሉ የልማት ስራዎች ተስፋ ሰጪ መሆኑን የገለፁ የጉብኝቱ ተሳታፊ የሚዲያ ባለሙያዎች በመንግስትና በህብረተሰብ ተሳትፎ የሚከናወኑ ተግባራትን የማስተዋወቁን ስራ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።
የሚዲያ ተቋማትና ባለሙያዎች አሰባሳቢ ትርክቶች የበላይነት እንዲይዙ ከማስቻልም ባለፈ በአገር አንድነትና ሰላም ላይ ያላቸውን ከፍተኛ ሚና በአግባቡ ለመወጣት በቅንጅት ልሰሩ እንደሚገባም ተብራርቷል።
በጉብኝቱ የደቡብ ምዕራብ ሚዲያ ኔትወርክ ሀላፊዎችና አጠቃላይ ሰራተኞች፣ የዳውሮ ዞን ፣ የወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች የመንግስት ኮሙኒኬሽን የስራ ሀላፊዎችና ባለሙያዎች እንዲሁም ሌሎች የባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
