“ትውልድን በስነምግባር ተቋምን በአሰራር” በሚል መሪ ሀሳብ አለምአቀፍ የስነምግባርና ፀረ-ሙስና ቀን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ታርጫ ከተማ እየተከበረ ይገኛል።

Spread the love

በዓሉ የሚከበረው በአለምአቀፍ ደረጃ ለ22ኛ ዙር፣በሀገርአቀፍ ለ21ኛ ዙር እንዲሁም በደቡብ ምዕራብ ለ4ኛ ዙር ነው።

በመድረኩ መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ም/ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ የተከበሩ አቶ ወንድሙ ኩርታ ለኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከትና ተግባር ለመውጣት በየተቋሙ የሚገኙ ባለድርሻ አካላት የሚጠበቅባቸውን ተግባር በመለየት ጠንክረው ሊሰሩ ይገባል ብለዋል።

በተጨማሪ እያንዳንዱ ግለሰብ ተጠያቂነትን በማስፈን ከውይይት ባለፈ በተግባር ሙስናን መከላከል ይጠበቅበታል ሲሉ ማሳሰባቸዉን የደቡብ ምዕራብ ሚዲያ ኔትወርክ ዘግቧል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *