በክልል ማዕከል አጠቃላይ 59 አመራሮችን ከኃላፊነት የማንሳት፣ የማሸጋሸግ እና በአዲስ መልክ ማደራጀት ሥራ ተሠርቷል፦አቶ ፍቅሬ አማን

Spread the love

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን ክልላዊ የአመራር ግምገማና ምዘና መድረክን አስመልክቶ መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸው በብልጽግና ፓርቲ ምክር ቤት በተቀመጡ አቅጣጫዎች መሠረት ከክልል እስከ ታችኛው መዋቅር ያሉት አመራሮች የግምገማና የምዘና መድረክ በጥብቅ ዲስፕሊን በመምራት አመራሩን በተገቢው መመዘን መቻሉን አስታውሰዋል።

ግምገማው የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምን መነሻ በማድረግ የ2018 የፓርቲና የመንግስት ድርብና ድርብርብ ተልዕኳዎችን ማስፈጸምና መፈጸም የሚችሉ አመራሮችን ለመፍጠር ከወትሮው በተለየ መልኩ የክልሉን ነባራዊ ሁኔታን ያገናዘበ ጥልቀት ያለው ሰነድ በማዘጋጀት ችግሮችንና ጥንካሬዎችን በሚዛኑ በማሳየት የአመራር ግምገማና ምዘና መካሄዱን ተናግረዋል።

ይህንን ግምገማ መነሻ በማድረግ ተልዕኮዎችን በቁርጠኝነት መፈጸምና ማስፈጸም የሚችል የአመራር ስምሪት በአዲስ መልክ ማዋቅር መቻሉን አቶ ፍቅሬ አብራርተዋል።

በዚህም በክልል ማዕከል በተደረገው ግምገማ ወንድ 10 ሴት 5 በድምሩ 15 አመራሮች ሙሉ በሙሉ ከኃላፊነተቻው የተነሱ ሲሆን በሽግሽግ ወንድ 18 ሴት 6 በድምሩ 24፣ በአዲስ መልክ ወደ ክልል አመራርነት የተቀላቀሉ ወንድ 18 ሴት 2 ድምር 20 በአጠቃላይ 59 አመራር ከኃላፊነት የማንሳት፣ የማሸጋሸግ በአዲስ መልክ ወደ መዋቅር የመቀላቀል ስራዎች በስፋት መሰራቱን ነው አቶ ፍቅሬ አማን ያብራሩት።

ይህ ስምሪቱ የአመራርን ውጤታማነት፣ ስነ ምግባርን እና ዝግጁነትን መሠረት በማድረግ በጥልቀት የተገመመገመ መሆኑን ጠቁመዋል።

አመራሩን ከውጤታማነት አንጻር የፓርቲና የመንግስት ተልዕኮዎችን በተገቢው ከመፈጸም ከማስፈጸም አንጻር ህዝቡ በብልጽግና ፓርቲ እንዲፈቱለት የሚፈልገው የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ከመመለስ አንጻር ግምገማው በጥልቀት መገምገሙን ጠቁመዋል።

ፓርቲያችን አሁን የደረሰበትን ደረጃ የሚመጥንና ቀጣይ ተልዕኮን በብቃት ለመፈፀም የሚያስችል ጠንካራ አመራርና ለመፍጠር የተረገ ግምገማ መሆኑን ገልጸዋል።

አዲስ የተሾሙና የተሸጋሸጉ አመራሮች መንግስትና ህዝብ የጣለባቸውን ኃላፊነት ተነሳሽነት በላቀ ብቃትና ተልዕኮዎችን በብቃት እንዲወጡ አሳስበዋል።

በፍቅር ከበደ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *