ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ በሚዛን አማን ከተማ እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ስራ ተዘዋውረው ተመለከቱ።

Spread the love

‎ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ በአማን ከተማና በሚዛን ከተማ በምዕራፍ ሁለት እየተሰራ ያለውን የኮሪደር ልማት ስራ ምልከታ አድርገዋል።

‎በጉብኝቱ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ፣ የክልሉ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማንን ጨምሮ የፌደራል እና የክልል እንዲሁም የዞንና የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር አመራሮች ተገኝተዋል።

‎በሚዛን አማን ከተማ እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ስራዎች በጥራት ስለመሰራቱ የጥራት ቁጥጥር ኮሚቴዎች ገለጻም አድርገዋል።

‎ህብረተሰቡ ለልማቱ ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ ሙሉ ፈቃደኛ ሆነው እየተባበሩ ስለመሆኑም ኮሚቴዎች ተናግረዋል ።

‎ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ የኮሪደር ልማት ስራው በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን በመረዳት በተጀመረው ፍጥነትና ጥራት ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል ሲል የቤንች ሸኮ ቴሌቪዥን ዘግቧል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *