ታዋቂ አርቲስቶችና የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች የተለያዩ የልማት ስራዎችን ለመመልከት ኮንታ ዞን ደርሰዋል

Spread the love

በሀገር ደረጃ ለ3 ተከታታይ ቀናት ከኪነጥበብ ባለሙያዎች ጋር ውይይት ተደርጎ እንደ ሀገር እየተሰሩ ያሉ የልማት ስራዎችን ምልከታ ለማድረግ እንደሆነ ለማድረ ያለመ መሆኑን የክልሉ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፋንታሁን ብላቴ ገልጸዋል።

ባለሙያዎቹ ወደ ኮንታ ዞን ኮንታ ኮይሻ አየር ማረፊያ ሲደርሱ ደማቅ አቀባበል የተደረገላቸው ሲሆን በአቀባበል ወቅት የዞን አመራር አካላትና የሀገር ሽማግሌዎች ተገኝተዋል።

ባለሙያዎቹ በቆይታቸው በዞኑ ውስጥ እየተሰሩ ያሉ የተለያዩ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችንና ሌሎች የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎችን ይጎበኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።

የልሉ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ በሆኑት በአቶ ፋንታሁን ብላቴ የተመራው የኪነጥበብ ባለሙያዎች ቡድን ኮንታ ዞን መግባታቸዉን የ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት መረጃ ያመለክታል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *