የእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጊዲዮን ሳር በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት ያደርጋሉ

Spread the love

የእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጊዲዮን ሳር በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ለማድረግ ዛሬ አዲስ አበባ ገብተዋል።

ጊዲዮን ሳር ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርሃኑ ፀጋዬ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ሚኒስትሩ በጉብኝታቸው የኢትዮጵያ እና እስራኤልን የሁለትዮሽ ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ከኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናት ጋር ውይይቶችን ያደርጋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *