የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ጥያቄዎችን እያቀረቡ ነው

Spread the love

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ስብሰባ እየተካሄደ ነው፡፡

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምላሽና ማብራሪያ ቢሰጥባቸው ያሏቸውን ጥያቄዎችና አስተያየቶችን እያቀረቡ ነው፡፡

ከቀረቡት ጥያቄዎች መካከልም፡-

• በአማራ ክልል ካለው ወቅታዊ ሁኔታ ጋር በተያያዘ ዘላቂ ሰላምን ከማረጋገጥ አኳያ ያለው ሁኔታ ምን ይመስላል?

• አለመግባባቶች ወደ ግጭት ከመግባታቸው በፊት የመንግሥት ዝግጁነት እንዴት ይገለጻል?

• የውጭ ጣልቃ ገብነትን በመመከት ረገድ ምን እየተሠራ ነው?

• የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅና አዳዲስ በመጀመር የሕዝብን ጥያቄ ለመመለስ በመንግሥት በኩል ምን እየተሠራ ነው?

• እንደ ሀገር ካለው የባሕር ወደብ ፍላጎት ጋር በተያያዘ አንዳንድ ብዥታዎች ስላሉ ግልጽ ለማድረግ ያህል ማብራሪያ ቢሰጥ፣

• በአጠቃላይ ፀረ-ሌብነት ትግልን ከማጠናከር በተለይም አንዳንድ ለብልሹ አሠራር የሚያጋለጡ ዘርፎችን ከሌብነት በጸዳ ሁኔታ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ እንደመንግሥት ያለው ቁርጠኝነት ቢገለጽ፣

• ለሀገራዊ ምክክሩ ሂደት ስኬት የመንግሥት ድጋፍ ቢጠቀስ፣

• የፕሪቶሪያው ስምምነት አፈጻጻም በምን ደረጃ ላይ ነው የሚገኘው የሚሉና ሌሎች ማብራሪያና ምላሽ ያስፈልጋቸዋል ያሏቸውን ጥያቄዎች የምክር ቤቱ አባላት በማቅረብ ላይ ይገኛሉ ሲል ኤፍቢሲ ዘግቧል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *