




በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ2ኛ ዙር የሚሰጠው የአንደኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ የስድስተኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተና በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ሁሉም አካባቢ በይፉ ተጀምሯል፡፡
ፈተናው ከዚህ በፊት ሲሰጥ ከነበረበት ሂደት በተሻለ ሁኔታ ለመስጠት ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ፣ የፈተና አዘገጃጀትና አሰጣጥ ስታንዳርድ በጠበቀና ወጥ በሆነ መንገድ መዘጋጀቱ ኩረጃን በማስቀረት የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ እንዲቻል እየተሠራ ላለው ተግባር ጉልህ ሚና እንዳለው ተገልጿል።
ፈተናው በሠላም ተጀምሮ እንዲጠናቀቅ የባለድርሻ አካላት ክትትልና ቁጥጥር በማድረግ ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡም ጥሪ ቀርበዋል።
በክልሉ በሁሉም ዞኖች ባለፉት ሁለት ቀናት ሲሰጥ የቆየው የ8ኛ ክፍል ፈተና በሰላም መጠናቀቁ ይታወቃል።
