




የደቡብ ምዕራብ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት በተመረቀ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለ318 ደንበኞች የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጠቱን የክልሉ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ማዕከል ምክትል ስራ አስፈፃሚ አቶ አህመድን አወል ገልጸዋል
በማዕከሉ በገቡ በ5 የክልልና በ4 የፌዴራል ተቋማት ስር የሚገኙ 28 አገልግሎቶችን በተቀላጠፈ መልኩ በአንድ ማዕከል ለዜጎች እየተሰጠ መሆኑም ተጠቁሟል።
ማዕከሉ በተመረቀ በአጭር ጊዜ ውስጥ 318 አካላት የጤና ቢሮ፤ የንግድ ቢሮ፤ የኢትዮ ቴሌኮም፤ የፖስታ ቤት እና ገቢዎች ቢሮ አገልግሎት ያገኙ መሆናቸውንም አቶ አህመድን ገልጸዋል።
ማዕከሉ ከዚህ ቀደም ይስተዋሉ የነበሩ የዜጎች አገልግሎት አሰጣጥ ችግሮች ከመቅረፍ ባሻገር በቴክኖሎጂ የታገዘ ፈጣንና ዲጂታላይዝድ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ምክትል ስራ አስፈፃሚው ተናግረዋል።
ዜጎች ወደ ተቋሙ በመምጣት ጊዜ፣ ገንዘብና እንግልት የሚቀንሰውን የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተጠቃሚ መሆን አለባቸው ሲሉም አቶ አህመድን መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ሲል ደቡብ ምዕራብ ሚዲያ ኔትወርክ ዘግቧል።
