ርዕሰ-መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ከተለያዩ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ተቋማት ጋር እየተወያዩ ነዉ።

Spread the love

ውይይቱ በክልሉ ያለውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን ለመፍታት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ በተለይም የጤና፣ የግብርና፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና የሌሎችም ስራዎችን ውጤታማነት ለማረጋገጥ የሚያስችል መግባባት መፍጠርን ዓላማው ያደረገ ነው።

በውይይት መድረኩ የዓለም ጤና ድርጅት (WHO)፣ የተባበሩት መንግስታት የህፃናት መርጃ ድርጅት (UNICEF)፣ የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ (OCHA)፣ የተባበሩት መንግስታት የምግብ እና እርሻ ድርጅት (FAO) እና ሌሎችም የተ.መ.ድ. ተወካዮችና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በውይይቱ እየተሳተፉ ነዉ።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *