ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽንን በተመለከተ

ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን የተሻለ ስኬት እንዲያስመዘግበ የምክር ቤቱ አባላት ጠንካራ ድጋፍ ማድረግ ይገባቸዋል፡፡ ለታሃድሶ ኮሚሽንን እና ለሽግግር ፍትህም መሰል ድጋፍ መደረግ አለበት፡፡ ከዚህ ቀደም ከነበሩ ኮሚሽኖች ትምህርት በመውሰድ አሁን ያሉ እድሎችን መጠቀም ይገባል፡፡ ከዚህ አኳያ መንግስት እንደ አስፈጻሚ አካል የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡

Read More

የአማራ ክልል አሁናዊ ሁኔታን በተመለከተ

በአማራ ክልል ላይ ከየትኛውም መንግስት በላይ አሁን ያለው መንግስት በርካታ የልማት ስራዎችን እያከናወነ ነው፡፡ በክልሉ ታላላቅ የመንገድ፣ የኢንዱስትሪ የቱሪዝም ልማቶች እየተከናወኑ ነው፡፡ በዚህም ክልሉን የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው፡፡ የፋሲል ቤተ-መንግስት እየታደሰ ነው፤ በዋና ዋና ከተሞች የኮሪደር ልማት እየተከናወነ ነው፡፡ የመገጭ ግድብን 7 ቢሊዩን ብር መድበን ከበርካታ ዓመታት የግንባታ መቋረጥ በኋላ ቀን ከሌት እየገነባን ነው፡፡…

Read More

የኢትዮጵያን ዕዳ ከ10 በመቶ በታች ለማድረግ ይሰራል – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

በሚቀጥሉት ዓመታት የኢትዮጵያን ዕዳ ከ10 በመቶ በታች ለማድረግ እንደሚሰራ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ የብድር ጫና ከአጠቃላይ ሀገራዊ ጥቅል ምርት አንጻር ከነበረበት ከ30 ነጥብ 6 በመቶ ወደ 13 ነጥብ 7 በመቶ ዝቅ ማድረግ መቻሉንም ጠቁመዋል፡፡ በሚቀጥሉት ዓመታት ይህን አሃዝ ከ10 በመቶ በታች ለማድረግ እንደሚሰራም አስታውቀዋል፡፡ ባለፉት ስድስት ዓመታት መንግስት ምንም አይነት የንግድ ብድር…

Read More

የስራ እድል ፈጠራን በተመለከተ

በተያዘው በጀት ዓመት ለ4 ነጥብ 3 ሚሊዮን ዜጎች የስራ እድል ለመፍጠር እቅድ ተይዟል፡፡ከዚህም ውስጥ 700 ሺህ ለሚሆኑት የውጭ ሀገር የስራ ስምሪት ለመፍጠር እቅድ የተያዘ ሲሆን፤ ባለፉት ሶስት ወራት ለሰለጠኑ ለ100 ሺህ ዜጎች በውጭ ሀገር የስራ ስምሪት ተፈጥሯል፡፡ ኮዲንግ እና የመረጃ ትንተናን ጨምሮ በርቀት ስራዎች ደግሞ ለ26 ሺህ ዜጎች የስራ እድል ተፈጥሯል፡፡

Read More

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች የሰጡት ማብራሪያ፦ክፍል አንድ

ሀገራዊ ሪፎርምን በተመለከተበተለያዩ ዘርፎች ሲከናወኑ የነበሩ ሪፎርሞችን አጠናቀን ሀገራዊ ማንሰራራት የምንጀምርበት ዘመን የመጀመሪያ ምእራፍ ላይ ተገኝተናል፡፡ በመሆኑም በ2017 በሁሉም ዘርፎች ተጨባጭ ለውጥ የምናስመዘግብ ይሆናል፡፡ ከዚህ አኳያ ከትናንት እሳቤ ወጥተን በጋራ ወደ ነገ መሻገር አለብን፡፡ ኢኮኖሚያዊ እድገትን በተመለከተበ2016 በጀት ዓመት በኢትዮጵያ 8 ነጥብ 1 በመቶ እድገት ተመዝግቧል፡፡ ይህ በዓለም አቀፍ ደረጃም ትልቅ ስኬት ነው፡፡ በዘንድሮው በጀት…

Read More

የኑሮ ውድነትን በተመለከተ

የኑሮ ውድነትን በዘላቂነት መቅረፍ የምንችለው ምርታማነትን በመጨመር ነው፡፡ የንግድ ስርዓቱን ማዘምንም ከፍተኛ ፋይዳ አለው፡፡ የኑሮ ውድነቱ እጅ አጠር ዜጎች ላይ ጫና እንዳይፈጥር መንግስት ከ300 እስከ 400 ቢሊዮን ብር የድጎማ በጀት መድቧል፡፡ ማዕድ ማጋራት፣ ትምህርት ቤት ምገባ እና እሁድ ገበያ መንግስት አቅመ ደካሞችን ለማገዝ የሚያደርገው ጥረት አካል ነው፡፡ በሀገር አቀፍ ደረጃም 249 ሺህ አቅመ ደካማ ዜጎች…

Read More

የመንግስት ገቢን በተመለከተ

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ የመንግስት ገቢ በእጅጉን ጨምሯል፡፡ ባላፉት ሶስት ወራት 180 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ ተችሏል፡፡ ይህም ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጻር የተሻለ እድገት የተመዘገበበት ነው፡፡ በ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ሶስት ወራት የተሰበሰበው ገቢ 109 ቢሊዮን ብር ብቻ ነበር፡፡ ነገር ግን ኢትዮጵያ ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ጥቅል ምርት አንጻር አሁንም ዝቅተኛ ገቢ የምትሰበስብ…

Read More