የዓድዋ ድል የሕብረብሔራዊ አንድነት መገለጫ የጥቁር ህዝቦች በዓል ነው፦ ክቡር አቶ ማስረሻ በላቸው።

128ኛው የዓድዋ በዓል”ዓድዋ የጥቁር ህዝቦች ድል”! በሚል መሪ ቃል በቦንጋ ከተማ እየተከበረ ነው። በክብረ በዓሉ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው የዓድዋ ድል በዓል የሕብረብሔራዊ አንድነት መገለጫ የጥቁር ህዝቦች በዓል ነው ሲሉ ተናግረዋል ። የዓድዋ ድል ኢትዮጵያዊያን የሕብረብሔራዊ ማህተማቸው ሆኖ የቆየ በዓል መሆኑንም ተናግረዋል ። የማይቻለውን እንሚቻል ያረጋገጠ…

Read More

2 ሺህ የሚሆኑ የቅድመ ወሊድና የወሊድ አገልግሎት መስጫ ማዕከላትን በኢትዮጵያ ለመገንባት የሚያስችል የሶስትዮሽ የመግባቢያ ስምምነት ተፈረመ፡፡

ስምምነቱን ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ እና በሩሲያ የፓን አፍሪካ የመንግስትና የግል አጋርነት የልማት ማዕከል ናቸው የተፈራረሙት፡፡ ስምምነቱ የእናቶችንና የጨቅላ ህፃናትን ህይወት ለማሻሻል የሚረዳ በአይነቱ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ‘ሚድ ዋይፈሪ’ ማዕከል እንደሚሆን ተጠቅሷል፡፡ የሩሲያው የፓን አፍሪካ የመንግስትና የግል አጋርነት የልማት ማዕከል ወደ ሀገር እንዲመጣ የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ላበረከተው አስተዋፅኦ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ…

Read More

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በ55 ሚሊዮን ዶላር ያስገነባውን የኢ-ኮሜርስ ሎጂስቲክስ ማዕከል አስመረቀ::

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ በ55 ሚሊዮን ዶላር ያስገነባውን ዘመናዊ የኢ-ኮሜርስ ሎጂስቲክስ ማዕከል በዛሬው ዕለት አስመርቋል። አየር መንገዱ በዛሬው ዕለት ያስመረቀው መሠረተ ልማት በአፍሪካ በዓይነቱ የመጀመሪያው ነው ተብሏል። በልዩ ሁኔታ ለኢኮሜርስ ሸቀጦች እንዲሁም ለፖስታ እና ጥቅል መልእክቶች የሎጂስቲክስ አገልግሎት ለመስጠት ታስቦ ወደ ስራ የሚገባው መሰረተ-ልማት፤ የአፍሪካን የኢኮሜርስ ኢንደስትሪ ዕድገት ከማፋጠኑም ባሻገር፣ አዲስ አበባን በአፍሪካ ብሎም በዓለም…

Read More

የአድዋ ድል የአብሮነት፣ የአንድነትና የጥቁር ህዝቦች የነፃነት ተምሳሌት የሆነ አሰባሳቢ ታሪካችን ነው:- አቶ ቀጀላ መርዳሳ

የአድዋ ድል የአብሮነት፣ የአንድነትና የጥቁር ህዝቦች የነፃነት ተምሳሌት የሆነ አሰባሳቢ ታሪካችን ነው ሲሉ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ቀጀላ መርዳሳ ተናገሩ። የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን 128ኛውን የአድዋ በዓልን “አድዋ የጥቁር ህዝቦች ድል” በሚል መሪ ሀሳብ አክብሯል። የመታሰቢያ በዓሉ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር አቶ ቀጀላ መርዳሳ ፣የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ወርቅነሽ ብሩ፣ የተቋሙ ሰራተኞችና አባት…

Read More

የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ሳምንት አውደ-ርዕይ ትውልድ ተሻጋሪ የሆኑ ሥራዎችን ሰንዶ ማስቀመጥ የተቻለበት ነው-አምባሳደር ብርቱካን አያኖ::

የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ሳምንት አውደ-ርዕይ ለቀጣይ የዲፕሎማሲ ሥራ ትውልድ ተሻጋሪ የሆኑ ሥራዎችን ሰንዶ ማስቀመጥ የተቻለበት መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ ገለጹ። አውደ-ርዕዩ ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲው መስክ ብሔራዊ ጥቅሟን አስከብራ ለመዝለቅ ያደረገችውን ጉዞ እና ዲፕሎማሲያዊ ከፍታዋን ያሳየ መሆኑንም ተናግረዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ብርቱካን አያኖ፤ የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ሳምንት አውደ-ርዕይን አስመልክተው ለመገናኛ ብዙኃን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።…

Read More