admin123

በጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ የተመራ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በ73ኛው የአፍርካ አህጉር የአለም ጤና ድርጅት መድረክ ላይ እየተሳተፈ ነው።

በዛሬዉ ዕለት በቦትሰዋና ጋባሮኒ የተጀመረዉ 73 ኛው የአፍርካ አህጉር የአለም ጤና ድርጅት መድረክ ላይ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን እየተሳተፈ ይገኛል። ይህ 73 ኛው የአፍሪካ አህጉር ከዓለም ጤና ድርጅት ስድስት የአህጉራዊ አስተዳደር አካላት አንዱ ሲሆን 47 አባል ሀገራት ያሉት የአፍሪካ ክልል ሀገራት የሚወክሉበት ኮሚቴ ነው፡፡ በመድረኩም ከ20 በላይ የሚሆኑ የተለያዩ የጤና አጀንዳዎች ላይ ዉይይት የሚደረግ ሲሆን የ2023…

Read More

የ2016 ዓ.ም የተማሪዎች ምዝገባ ቦንጋ ከተማ በሁሉም ትምህርት ቤቶች ከጠዋት 2 ስዓት ጀምሮ በይፋ ተጀምሯል

በቦንጋ ከተማ አስተዳደር ስር የሚገኙ ት/ቤቶች የ2016 ዓ.ም የተማሪዎች ምዝገባ በይፋ ተጀምሯል። ምዝገባ ላይ እያሉ ያነጋገርናቸው የቢሻው ወ/ዮሐንስ 2ኛ ደረጃና መሠናዶ ትምህርት ቤት ተማርዎች ዛሬ በይፋ በጀመረው ምዝገባ ዕለተ በመገኘታቸው መደሰታቸዉን ገልፆ በመስከረም 03/2016ዓ.ም በሚጀምረው መደበኛ ትምህርት በነቃ ሁኔታ ትምህርታቸውን እንደሚጀምሩም ተናግረዋል:: ወላጆቻቸዉም በበኩላቸው የትምህርት ጉዳይ የትምህርት አካላት ብቻ ሳይሆን የወላጆችንም ድጋፍ የሚጠይቅ በመሆኑ ተማሪዎችን…

Read More

የሸካ ዞን ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል ።

ምክርቤቶች የህዝብ ሉአላዊነት መገለጫ እንደመሆናቸው መጠን የህዝብ ልማት ፣ ሰላምና የመልካም አሰተዳደር ችግሮች መፈታታቸው ክትትል ያደርጋሉ ያሉት የሸካ ዞን ምክር ቤት ዋና አፌ -ጉባኤ የተከበሩ አቶ ዮሐንስ ካሳሁን ምክር ቤቱ በ2015 በጀት ዓመት በሰክተሮች ክትትል እና ቁጥጥር ስራን በማጠናከር የተግባር አፈፃፀም ዉጤታማ እንዲሆን ዘርፈ ብዙ ተግባራትን ማከናወኑን ገልፀዋል። በበጀት ዓመቱ በዞኑ በርካታ የልማትና መልካም አስተዳደር…

Read More

ጉርጉቶ /የእግዜር ድልድይ

ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጽያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ከካፋ ዞን ከቦንጋ ከተማ በ12 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ወደ ጠሎ ወረዳ በሚወስደው መንገድ ከማኪራ ጥቅጥቅ የተፈጥሮ ቡናና ደን በቅርብ ርቀት ላይ ይገኛል። ፈፅሞ የሰው የእጅ ፈጠራና ልፋት ሳይዳስሰው በተፈጥሮ በፈጣሪ ጥበብ የተሰራ ድንቅ ድልድይ ነው። ጉርጉቶ የእግዜር ድልድይ! ይህንን ድንቅ የቱሪስት መስህብ በየአመቱ የአገር ውስጥና የውጭ አገር ጎብኚዎች ይጎበኙታል።…

Read More

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ከመከላከያ ሠራዊት አመራሮች ጋር መክረዋል ።

ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ክልላዊ የጸጥታ ሁኔታን የተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል ። በክልሉ አሁን ላይ አንጻራዊ ሠላም መኖሩንና ይህንንም በዘላቂነት ማስቀጠል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት አድርገዋል። ክልሉ ከደቡብ ሱዳን ጋር በሚዋሰንባቸው የድንበር እንዲሁም በአርብቶ አደር አካባቢዎች የሚከሰተው የጸጥታ ችግር በዘላቂነት በሚፈታበት ሁኔታ ከመከላከያ ሠራዊት አመራሮች ጋር መክረዋል ። የክልሉ ሠላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አንድነት አሸናፊ…

Read More

በኮንታ ዞን በ50 ሄክታር ማሳ ላይ የመስራች ዘር ብዜት ሥራ እየተከናወነ ነው።

በክልሉ ግብርና ቢሮና የምርምር ኢንስቲትዩት አስተባባሪነት በኮንታ ዞን ‘የመስራች ዘር’ ብዜት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው በተገኙበት ተጀምሯል። በክልሉ ምርምር ኢኒስቲትዩት የታርጫ ምርምር ማዕከል በኮንታ ዞን አመያ ዙሪያ ወረዳ ሼታ ቀበሌ በ50 ሄክታር መሬት ላይ የስንዴና ባቄላ ዘር ብዜት የክልል፣ የዞንና የወረዳው አመራሮችና የአከባቢው ነዋሪዎች በተገኙበት በይፋ ተበስሯል። የተዘራው ‘መስራች…

Read More

ከደረጃ “ሐ” ግብር ከፋዮች ከ229 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰብስቧል – ወ/ሮ ህይወት አሰግድ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ህይወት አሰግድ በወቅታዊ የገቢ አሰባሰብ ሂደትን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በክልሉ ከመነሻው ጀምሮ ሁሉን ባሳተፈ ሁኔታ ከክልል ጀምሮ በየደረጃው አስፈላጊውን መድረክ በመፍጠር በሁሉም ዞኖች የደረጃ “ሐ” የዕለት ገቢ ግመታ ስራ እና የአሰባሰብ ስራዉ በስኬት መጠናቀቁን ተናግረዋል። በተለያዩ ምክንያቶች በየሶስት ዓመቱ መገመት የነበረበት የደረጃ “ሐ” ግብር ከፋዮች…

Read More

በአከባቢው ያለውን የደን ሀብት በተገቢው መንከባከብና መጠበቅ ይገባል፦ ዶክተር ፍቅሩ ረጋሳ

የኢፌዴሪ ግብርና ሚኒስቴር አመራሮች እና ባለሙያዎች በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ካፋ ዞን በመገኘት ሁለተኛ ዙር አረንጓዴ አሻራ የማሳረፍ መርሀ ግብር አከናውነዋል። በክልሉ ካፋ ዞን ጊምቦ ወረዳ ምቺት ቀበሌ በተካሄደው የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ላይ ሚኒስትር ደኤታዎችና ሰራተኞች ተሳትፈዋል። የግብርና ሚኒስቴር የእንስሳት እና ዓሣ ሀብት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ፍቅሩ ረጋሣ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ…

Read More

እናቶችንና አቅመ ደካሞችን መርዳትና ማገዝ ሀገርን መርዳትና ማገዝ ነው ፦ ክቡር አቶ ጸጋዬ ማሞ

በአቶ ፀጋ ማሞ አስተባባሪነት በጉራፈርዳ ወረዳ ኦቱዋ ሴጋ ቀበሌ ነዋሪ ለሆኑ አቅመ ደካማ እናት የቤት መስሪያ ቁሳቁስና የገንዘብ ድጋፍ አድርገዋል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጸጋዬ ማሞ በሚዛን አማን ከተማ የሚገኙ ወጣቶችን በማስተባበር በጉራፈርዳ ወረዳ ሴጋ ቀበሌ ለሚገኙ አቅመ ደካማ እናት 24 ቆርቆሮ ፣ ምስማር ፣ ፍራሽ ፣ ብርድ…

Read More

ለሁለት ተከታታይ ቀናት በቴፒ ከተማ ሲካሄድ የነበረው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብሔረሰቦች ምክርቤት 1ኛ አመት 1ኛ መደበኛ ጉባኤ ተጠናቀቀ ።

ምክርቤቱ በዛሬው ውሎ የምክርቤቱ አባላት የአሰራርና የአባላት ሥነሥርዓት ለመደንገግ በወጣ ደንብ ላይ መክሯል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት የብሔረሰቦች ምክርቤት የአሰራርና የአባላት ሥነሥርዓት ለመደንገግ የወጣ ደንብ በአቶ መቱ አኩ ቀርቧል። የክልሉን ብሔረሰቦች ምክርቤት ሥልጣን እና ተግባርን ለመዘርዘር በወጣው አዋጅ ቁጥር 10/2014 አንቀጽ 43 መሠረት በማድረግ ደንቡ መዘጋጀቱን አቶ መቱ አኩ ገልጸዋል ። የተዘጋጀው ደንብ…

Read More