”አድዋ የመደመር ተምሳሌታዊ አርማ” በሚል መሪ ሀሳብ የፓናል ውይይት እየተካሄደ ነው

Spread the love

በፓናል ውይይቱ ላይ የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዶክተር ዓለሙ ስሜ፣ የመንግሥት ረዳት ተጠሪ ሚኒስትር ዴኤታ ረዳት ፕሮፌሰር ምህረቱ ሻንቆን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የፖሊስ መኮንኖች፣ የምክር ቤት አባላት፣ አርበኞችና ምሁራን ተገኝተዋል።

በኢዜአ አዲሱ ስቲዲዮ እየተካሄደ ባለው የፓናል ውይይት የአድዋ ድል የአብሮነትና የአንድነት ተምሳሌት፣ የጥቁር ህዝቦች ነፃነት የነበረው ሚና እንዲሁም የዚህ ዘመን አድዋ ምን መሆን አለበት በሚሉ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ፅሑፎች ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል።

128ኛው የአድዋ ድል በዓል በመጪው ቅዳሜ በተለያዩ ዝግጅቶች ይከበራል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *