ምክክሩ ኢትዮጵያውያን ችግሮቻቸውን በራሳቸው መፍታት እንደሚችሉ ማረጋገጫ ይሆናል፦ፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገ/ማርያም
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን እያካሄደ ያለው ምክክር ኢትዮጵያውያን ተነጋግረው የራሳቸውን ችግሮች ራሳቸው መፍታት እንደሚችሉ ማረጋገጫ ሊሆን እንደሚችል ፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገ/ማርያም ተናገሩ። እርሳቸው የተሳተፉበት የፌዴራል ተቋማት እና ማኅበራት የምክክር መድረክ ተሳተፊዎች ሀሳባቸውን ያለገደብ ማንሳታቸውንም ፕሮፌሰር ዓለማየሁ ጠቅሰዋል። በመድረኩ ላይ ሲሳተፉ የዳያስፖራውን ጉዳይ በስፋት ማንሳታቸውን ጠቅሰው፤ ዳያስፖራው የሀገር ኢኮኖሚን በመደገፍም ሆነ ሀገርን በመከላከል ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ስላለው በምክክሩ…
