Trendings

የኮንታ ዞን ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ መካሄድ ጀመረ።

Spread the love

የኮንታ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 7ኛ የስራ ዘመን 23ኛ መደበኛ ጉባኤ መካሄድ የጀመረ ሲሆን በጉባኤው የምክር ቤቱ የ2017 ዓ/ም የ6 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት፣ የአስፈፃሚዎች የ2017 ዓ/ም የ6 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት፣ የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የ2017 ዓ/ም የ6 ወራት አፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦ እንደሚፀድቅ ተገልጿል።

ጉባኤው ዛሬን ጨምሮ ለ2 ቀናት ቆይታ ሲያደርግ ሌሎችም በዞን መንግስት የተገዙ የግንባታ ማሽን መተዳደሪያ ሞሽን፣ በ2016 ዓ/ም የተሰበሰበ ትርፍ ገቢ ረቂቅ በጀት እና የተለያዩ ሹመቶች ቀርበው እንደሚፀድቁም ይጠበቃል።

የዞኑ ም/ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ ብርሃኑ አቱሞ በጉባኤው መክፈቻ ንግግራቸው ም/ቤቱ ከፍተኛ የፖለቲካ ስልጣን ባለቤትና ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ዋነኛ ተቋም መሆኑን ገልፀው ይህንንም ኃላፊነት ለመወጣት እየሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

በዞኑ በቀጣይ የቀበሌ ም/ቤቶች ጉባኤ ማጠናከር፣ የኦዲት ግኝት ዕዳ አመላለስ ማጠናከርና መሠል ጉዳዮች በትኩረት የሚከናወኑ መሆናቸውን የኮንታ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት መረጃ ያመለክታል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *