ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) የዴንማርክ እና የኖርዌይ አምባሳደሮችን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) የዴንማርክ እና የኖርዌይ አምባሳደሮችን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። አምባሳደሮቹ በክልሉ በሁለቱ መንግሥታት ድጋፍ በደንና አከባቢ ጥበቃ እየተከናወነ ያለውን ተግባር ለመመልከት እንዲሁም በቀጣይ ፕሮግራሞችን ማስቀጠል በሚቻልበት አግባብ ከክልሉ መንግሥት ጋር ምክክር ለማድረግ መሆኑ ተገልጿል። የክልሉ አብዛኛው ማህበረሰብ ኑሮው በደን ጥገኛ መሆኑን የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ የደን…
