ጉርስና ጥሪት በካሳቫ
ካሳቫ የሚመደበው ከቁልቋል (Euphorbiaceae) ቤተሰብ ሲሆን ከ200 በላይ የሆኑ ዝርያዎች አሉት፡፡ ሳይንሳዊ ስያሜው (Manihot esculenta) ይባላል፡፡ በፖርቹጋል ነጋዴዎች አማካይነት መጀመሪያ በ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በቤንን ባህረሰላጤና በኮንጎ ወንዝ አድርጎ ወደ ምዕራብ አፍሪካ እንደ ገባ ይታወቃል፡፡ ለሁለተኛ ጊዜ ወደ 18ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ በሪየኒየን፣ በማዳጋስካርና በዛንዚባር ወደቦች አድርጎ ወደ ምስራቅ አፍሪካ እንደ ገባ መዛግብት…
