የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ፎረም በደቡብ ኮሪያ ተካሄደ

ከ200 በላይ የሚሆኑ የኩባንያ ባለቤቶች በተገኙበት የኢትዮጵያን እምቅ የኢንቨስትመንት እድል ለኢንቨስተሮች የሚያስተዋውቅ ፎረም በደቡብ ኮሪያ ሴዑል ተካሂዷል፡፡ በዝግጅቱ ላይ በደቡብ ኮሪያ የኢትዮጵያ ልዩ መልዕክተኛ እና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ደሴ ዳልኬ÷ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የተሻለ የኢንቨስትመንት አማራጮች እና ማበረታቻዎች እንዳላት አስገንዝበዋል፡፡ በኢትዮጵያ ምቹ የኢንቨስትመንት ምህዳር ለመፍጠር በመንግስት የተደረጉ ፖሊሲ ማሻሻያችን፣ የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት ማበረታቻዎች እና ምቹ የንግድ…

Read More

ከተሞች ለነዋሪዎች የተመቹ እንዲሆኑ የተጀመሩ ጥረቶች ለውጥ እያመጡ መሆናቸውን የደካ እና ጀሙ ከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች ገለጹ

ደካ እና ጀሙ ከተማ አስተዳደሮች በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግሥት በካፋ እና ምዕራብ ኦሞ ዞኖች ከሚገኙ ከተማ አስተዳደር መዋቅሮች መካከል ተጠቃሾች ናቸው። ሁለቱ ከተማ አስተዳደር መዋቅሮች በ2013 ዓ.ም በፈርጅ ሶስት የታቀፉ ከተሞች ሲሆኑ እነዚህን ከተሞችን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ ሰፊ ሥራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ። የደካ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ በላይ ባደገ እንደገለጹት፤ ደካ ከተማን ለነዋሪዎች ለመኖሪያ…

Read More

የማህበረሰብ ተሳትፎን በማሳደግ በሽታን መከላከል ይገባል – ዶ/ር መቅደስ ዳባ

የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ከሌሎች የስራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን ከጌትስ ፋውንዴሽን የጤና ቡድኖች ተወካዮች ጋር ተወያይተዋል። በመድረኩ የጤና ሚኒስቴር ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ማብራሪያ የሰጡት ዶክተር መቅደስ፥ በአጋሮች የሚተገበሩ ፕሮግራሞች ከጤና ሚኒስቴር እና ብሔራዊ ስትራቴጂዎች ጋር የተናበቡ መሆን አለባቸው ብለዋል። የእናቶችና ህጻናት ጤና እና የመጀመሪያ ደረጃ ጤና ክብካቤ አገልግሎትን ማሳደግ ጤና ሚኒስቴር ቅድሚያ…

Read More

ብልፅግና ፓርቲ በ2ኛ ጉባኤው ባሳለፋቸው ውሳኔዎች ዙሪያ ከዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት ጋር እየተወያየ ነው

በብልጽግና ፓርቲ በሁለተኛ መደበኛ ጉባኤው ባሳለፋቸው ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ዙሪያ ተቀማጭነታቸውን አዲስ አበባ ካደረጉ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት ጋር ውይይት እያካሄደ ነው። በፓርቲው ዋና ጽህፈት ቤት እየተካሄደ ባለው ውይይት ላይ አምባሳደሮችና የዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች ተገኝተዋል። የብልጽግና ፓርቲ የህዝብ እና ዓለም አቀፍ ግንኙት ዘርፍ ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) እንደገለጹት፥ፓርቲው በ2ኛ ጉባኤው የዜጎችን ተጠቃሚነት ከፍ የሚያደርጉ ውሳኔዎችን አሳልፏል።…

Read More

ቴክኖሎጂን የችግር መፍቻ ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ – ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር)

ቴክኖሎጂን ለህዝባችን ችግር መፍቻ እና የእድገታችን ማፍጠኛ ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ሲሉ የአርተፊሻል ኢንተለጀንስ ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) ገለጹ። ባለፉት ሦስት ዓመታት ለሀገረ መንግስት ግንባታ መሰረት የሚጥሉ ነፃ፣ ገለልተኛና ብቃት ያላቸውን ተቋማት የመገንባት ሂደት ዘርፈ ብዙ ውጤቶች ማስመዝገባቸውንም ተናግረዋል። በተቋማት ግንባታ ላይ በተለይ በቴክኖሎጂ ዘርፍ ከተሰሩ ሥራዎች መካከል ነባር ተቋሞችን አሰራርና አገልግሎታቸውን ማዘመን…

Read More

ህገወጥ የሰዎች ፍልሰትን ለመከላከልና ተጨባጭ ለውጥ ለማምጣት በትኩረት መስራት ይገባል ተባለ

ህገወጥ የሰዎች ፍልሰትን ለመከላከልና ተጨባጭ ለውጥ ለማምጣት በተለየ ትኩረት መስራት እንደሚገባ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግ እና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እፀገነት መንግስቱ አሳሰቡ። ብሔራዊና ክልላዊ የፍልሰት ትብብር ጥምረቶች የግማሽ ዓመት የስራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። በመድረኩ የተገኙት የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዋ÷ ህጋዊ ፍልሰት ለማጎልበት የተሰሩ ሥራዎች ውጤት እያስመዘገቡ ቢሆንም በህገወጥ መንገድ…

Read More

ሁሉንም የገቢ አርዕስቶች ለይቶ በአግባቡ በመሰብሰብ የህብረተሰቡን የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄ ለመመለስ መረባረብ ያስፈልጋል፦አቶ አበበ ማሞ

የሸካ ዞን ገቢዎች መምሪያ የ6 ወራት ዕቅድ አፈፃፀምና በቀሪ ወራት ትኩረት አቅጣጫ ዙሪያ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት የምክክር መድረክ በማሻ ከተማ እያካሄደ ይገኛል። የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ በመድረኩ ላይ ተገኝተው ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ገቢ ኢኮኖሚያዊ ፣ማህበራዊና ፖለቲካዊ ስራዎችን ለማሳካት ትልቅ ድርሻ አለው ብለዋል። በዞኑ በ2017 በጀት ዓመት ከ1.1 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ…

Read More

የሚዲያ ተቋማት ፈጣን ፣ ጥራትና ዘመናዊ የሚዲያ አስተዳደርን በማስፋት ለአድማጭ ተመልካቹ ተደራሽ ሊሆኑ ይገባል ፦ አቶ የሺዋስ ዓለሙ

የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ሚዛን ቅርንጫፍ ጣቢያ የ2017 የመጀመሪያ ግማሽ አመት ዕቅድ አፈጻጸም መድረክ በሚዛን አማን ተካሂዷል። የቅርንጫፍ ጣቢያው የልማት ዕቅድና በጀት አስተዳደር ባለሙያ አቶ መካሻው ከበደ ባቀረቡት የ6 ወራት ሪፖርት ጣቢያው በቤንች ሸኮና ምዕራብ ኦሞ ዞን በሚገኙ 5 ቋንቋዎች የሬዲዮና የቴሌቪዥን ስራ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። በግማሽ ዓመቱ በሬዲዮ ኬዝ 5ሺ 210 የሬዲዮ ዜናዎች ፣…

Read More

በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በጋራ የመስራት ፍላጎት እያሳዩ ነው – አቶ መስፍን ጣሰው

በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በአየር ትራንስፖርት ዘርፍ በጋራ የመስራት ፍላጎት እያሳዩ መሆኑን የኢትዮያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ገለጹ። አየር መንገዱ በየጊዜው ዓለም አቀፍ አድማሱን በማስፋት ላይ መሆኑንም ተናግረዋል። የአፍሪካ አህጉርን ደግሞ በአየር ትራንስፖርት የማስተሳሰር ተግባሩን አጠናክሮ ቀጥሏል ነው ያሉት፡፡ በአሁኑ ወቅትም በርካታ የአፍሪካ ሀገራት በአየር ትራንስፖርት ዘርፍ…

Read More

“ሪፖርታዥ”

ፋና ወጊው “የእሞታ” አዳሪ ትምህርት ቤት ኮንታ ዞን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ከሚገኙ ስድስት ዞኖች አንዱ ነው ። ዞኑ የተለያዩ የተፈጥሮ ሀብት ለም መሬት፣ ቱባ ባህልና የቱርስት መዳረሻዎች ያሉበት ለዓይን የሚማረክ የጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ እና በገበታ ለሀገር የተሰራ የዝሆን ዳና ሎጅን ባለቤት መሆኑን ለአብነት መጥቀስ ይቻላል ። በዞኑ ውስጥ በማህበራዊ ልማት ዘርፍ…

Read More