በግንባታ ላይ የሚገኙ የንጹህ መጠጥ ዉሃ ፕሮጀክቶች በፍጥነት ተጠናቀዉ ለአገልግሎት እንዲበቁ እየተሰራ ነው፦ኢንጂነር በየነ በላቸው

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግሥት በ2017 በጀት ዓመት ባለፉት ወራት 61 የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ከ64ሺ በላይ ህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ማድረግ እንደተቻለ የክልሉ ውሃ፣ ማዕድና ኢነርጂ ቢሮ ገለጸ። የክልሉ ውሃ፣ ማዕድን እና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር በየነ በላቸው የተመራ ልዑክ በቤንች ሸኮ ዞን ሸኮ ወረዳ በግዝመሬት እና ሺሚ ቀበሌዎች በግንባታ ላይ የሚገኘው የንጹህ…

Read More

የሳይበር ደህንነትን የማስጠበቅ ሀገራዊ አቅም እያደገ መጥቷል – የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር

የሳይበር ደህንነትን የማስጠበቅ ሀገራዊ አቅም እያደገ መምጣቱን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሃሚድ ተናገሩ። ዋና ዳይሬክተሯ በተቋሙ የሪፎርም ስራዎች፣ እየተገኙ ባሉ ውጤቶና ቀጣይ በሚከናወኑ ተግባራት ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በማብራሪያቸውም የሳይበር ደህንነትን ማስጠበቅና የመከላከል አቅምን ማሳደግ የሚያስችሉ በርካታ የለውጥ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል። ከለውጥ ስራዎቹ መካከል የሳይበር ደህንነት ፖሊሲ ተዘጋጅቶ ስራ ላይ መዋሉን አስታውሰዋል። ኮምፒውተርን…

Read More

የአንድነታችን አርማ የሆነውን የዓድዋ ድል በኢኮኖሚው መስክ ለመድገም እየሠራን ነው – የታርጫ ከተማ ነዋሪዎች

የኢትዮጵያውያን ኅብረ ብሔራዊ አንድነት ዓርማ የሆነውን የዓድዋ ድል በኢኮኖሚው መስክ ዳግም ለማስመዝገብ እየሠራን ነው ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው በዳውሮ ዞን የታርጫ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። 129ኛው የዓድዋ ድል በዓል “ዓድዋ የጥቁር ህዝቦች ድል” በሚል መሪ ሀሳብ ይከበራል። ድሉን በማስመልከት ኢዜአ ያነጋገራቸው በዳውሮ ዞን ታርጫ ከተማ ነዋሪዎች ዓድዋ የኢትዮጵያውያን ዘመን አይሽሬ ጀግንነት ማሳያ ነው ብለዋል። አቶ በለጠ ባሾ…

Read More

የፓርቲው የኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን የስነ-ምግባር መከታተያ ክፍሎችን ማጠናከር ይገባዋል

የስነ-ምግባር መከታተያ ክፍሎች ተልዕኮአቸውን በአግባቡ እንዲወጡ የብልጽግና ፓርቲ የኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን ድጋፉን እንዲያጠናከር የፌዴራል ስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን አመለከተ። የፌዴራል ስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በየደረጃው ከሚገኙ የብልፅግና ፓርቲ የኢንስፔክሽንና ስነ ምግባር ኮሚሽን አባላትና አመራሮች ጋር በፀረ ሙስና ትግልና ስነ-ምግባር ግንባታ ላይ በትብብር መስራት በሚቻልበት ሂደት ላይ መክረዋል። የፌዴራል ስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽነር ሳሙኤል ኡርቃቶ (ዶ/ር)…

Read More

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በተለያዩ አካባቢዎች የእሳት አደጋ እየተከሰተ በመሆኑ ጥንቃቄ እንዲደረግ የክልሉ ደን፣ አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ቁጥጥር ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ኢንጂነር አስራት ገብረማርያም አሳሰቡ።

በክልሉ ከሽካ ዞን በስተቀር በአምስት ዞኖች ስፋቱና የጉዳቱ መጠን የተለያየ የደን እሳት ቃጠሎ መከሰቱን አስታውቀዋል። በካፋ ዞን በጠሎ እና በአዲዮ ወረዳዎች አዋሳኝ አካባቢ ደን ላይና በዴቻ ወረዳ ዳኪቲ ቀበሌ እንዲሁም በገዋታ ወረዳ የደን ቃጠሎ ተከስቶ ማህበረሰቡን በማስተባበር ለመቆጣጠር እየተሠራ ነው ብለዋል። በዳውሮ ዞን ማረቃ አደአ፣ ማሪ ወረዳ፣ ታርጫ ዙሪያ ወረዳ እና ሎማ ወረዳ የእሳት ቃጠሎ…

Read More

ከሸቀጦች የወጪ ንግድ ከ3 ነጥብ 84 ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ ተገኘ

ባለፉት ሰባት ወራት ከሸቀጦች የወጪ ንግድ ከ3 ነጥብ 84 ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ። ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ በሸቀጦች የወጪ ንግድ የእቅዱን 146 በመቶ መፈጸም መቻሉን አመልክተዋል። ለገቢው መገኘት ወርቅ፣ ቡና፣ የቅባት እህሎች፣ ኤሌክትሪክ እና የቁም እንስሳት ወጪ ንግድ ከእቅዳቸው በላይ ማስገኘት የቻሉ የወጪ ንግድ…

Read More

በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቤንች ሸኮ ዞን ተወካዮች ከዞኑ የካቢኔ አባላት ጋር በዞናዊ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት እያካሄዱ ነው።

የፓርላማ አባላቱ በቀጣይም በዞኑ በትምህርት ፣ ጤና ፣ የመንገድ እና የውሀ ልማት ስራዎችን ተዘዋውረው የሚጎበኙ ሲሆን ከወከሏቸው ህዝብ ጋር ውይይት እንደሚያደርጉም ገልጸዋል። የቤንች ሸኮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን እንደተናገሩት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዞኑ ተወካዮች በተለያዩ ጊዜያት ወደ ህዝቡ እየወረዱ የተለያዩ የልማት ስራዎችን የመጎብኘትና ከወከሉት ህዝብ ጋር መድረኮችን እየፈጠሩ መቆየታቸውን ገልጸዋል። የምክር ቤት…

Read More

የህዝብ ውይይት መድረኮችን በማጠናከር በከተሞች የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታት እንደሚገባ ተገለጸ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ በከተሞች የመልካም አስተዳደርና የልማት ተግባራት ላይ የተዘጋጀ የምክክር መድረክ በቦንጋ እያካሄደ ነው። በምክክር መድረኩ የተገኙት የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ ኢንጅነር የማታለም ቸኮል የመድረኩ ዓላማ ሀገራችን ለከተማ ልማት ከሰጠችው ትኩረት፣ ከከተሞች ተለዋዋጭ ባህሪና የህዝብ ቁጥር በየጊዜው ከመጨመር አንጻር ስራው ጊዜ የማይሰጥ በመሆኑ እስካሁን የመጡ ለውጦችን…

Read More

የብሔር ብሔረሰቦችን የማንነት መገለጫ ለማዘጋጀት የሦስትዮሽ ስምምነት ተፈረመ

የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦችን የማንነት መገለጫ ለማዘጋጀት የሚያስችል የሦስትዮሽ ስምምነት ተፈረመ፡፡ ስምምነቱን የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘዉ ተሻገር፣ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ እንዲሁም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ስምምነቱን ፈርመዋል። ስምምነቱ የኢቲኖግራፊና የቋንቋ ባህሪያትን ለማሰናዳት ያስችላል ተብሏል፡፡ አፈ ጉባኤ አገኘዉ ተሻገር፤ ስምምነቱ የብዝኃ ልሳንና ብዝኃ ባህል ባለቤት የሆነችዉን ኢትዮጵያን በውል…

Read More

የዓድዋ ድል የኢትዮጵያውያን ጀግንነትና ድል አድራጊነት በዓለም አደባባይ ከፍ ብሎ የታየበት ገድል ነው

የዓድዋ ድል የኢትዮጵያውያን ጀግንነትና ድል አድራጊነት በዓለም አደባባይ ከፍ ብሎ የታየበት የጥቁር ህዝቦች ገድል መሆኑን የታሪክ ምሁራን ገለጹ። ዓድዋ ላይ ጀግንነትን፣ ህብረ ብሔራዊ አንድነትና የአልገዛም ባይነት ወኔን ከጦርና ጎራዴ ጋር የታጠቁ ኢትዮጵያውያን በዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታገዘውን የጣሊያን ወራሪ ጦር ድል በማድረግ የሀገራቸውን ክብርና ሉዓላዊነት አጽንተዋል። የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም ኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን የመላው ዓለም…

Read More