በሰው መነገድና ሰውን በህገ ወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር ወንጀሎችን ለመከላከል በጋራ እየተሰራ ነው

በሰው መነገድና ሰውን በህገ ወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር ወንጀሎችን ለመከላከል በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን የፍትህ ሚኒስቴር አስታወቀ። ብሔራዊና ክልላዊ የፍልሰት ትብብር ጥምረት የ2016 በጀት ዓመት የዕቅድ ክንውንና ቀጣይ ትኩረት ላይ የባለድርሻ አካላት የውይይት መድረክ በአዳማ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በላይሁን ይርጋ በመድረኩ ላይ እንደገለፁት መደበኛ ባልሆነ መንገድ ከሀገር የሚወጡ ዜጎች ለተለያየ ሰብዓዊ መብት…

Read More

ከ550 ቢሊየን ብር በላይ ተጨማሪ በጀት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሊቀርብ ነው

ለ2017 በጀት ዓመት ከ550 ቢሊየን ብር በላይ ተጨማሪ በጀት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለማፀደቅ ዝግጅት መደረጉን ገንዘብ ሚኒስቴር ገለጸ። የ2017 የፌዴራል መንግሥት በጀት 971 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ሆኖ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጽደቁ ይታወሳል። በጀቱ ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ21 ነጥብ 1 በመቶ እድገት ያሳየ ነበር። ከዚህ ውስጥ ለመደበኛ በጀት 451 ነጥብ 3 ቢሊየን…

Read More

ለ22 የከርስ ምድር ውሃ ፕሮጀክቶች የኮንትራት ውል ተፈጽሞ ወደ ሥራ መገባቱ ተገለጸ

ባለፉት ስድስት ወራት ለ22 የከርስ ምድር ውሃ ፕሮጀክቶች የኮንትራት ውል ተወስዶ ወደ ሥራ መገባቱን የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ ሚኒስቴሩ የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት አፈጻጸምን ከክልል የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን እንዲሁም ከፕሮጀክቱ ተወካዮች ጋር እየገመገመ ነው፡፡ የውሃ ኢነርጂ ሚኒስትር አማካሪ ሞቱማ መቃሳ ÷ከሁለት ዓመት በፊት የተጀመረው የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት ከሰው ሃይል ማሟላት…

Read More

የክልሉ ጸጥታ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ በማካሄድ የተለያዩ አቅጣጫዎችን አስቀመጠ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል፥የፀጥታ ጋራ ምክር ቤት ጉባኤ በክልሉ ነባራዊ የፀጥታ ሁኔታዎችና የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎች ላይ በሚዛን አማን ከተማ መክሯል። በክልሉ የፀጥታ ችግር በነበረችው አከባቢዎች በተሰራው ጠንካራ ስራ አመርቂ ውጤት መመዝገቡን ምክር ቤቱ ገምግሟል። በክልሉ የፀጥታ ችግር በነበረባቸው አርብቶአደር ቀጠናዎች በቅንጅት በተሰራው ውጤታማ ሥራ ተቋርጦ የነበረውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ዳግም ማስቀጠል መቻሉ በምክር ቤቱ…

Read More

ለረዥም ዓመታት የመልካም አስተዳደር ጥያቄ የነበሩ ሁለት የድልድይ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ተመረቁ።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል፥ በቤንች ሸኮ ዞን የተገነቡ የአጉና እና የዳማ ወንዝ ድልድይ ግንባታ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) እና ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ተመርቀው ለአግልግሎት ክፍት ሆነዋል። በክልሉ መንገዶች ባለስልጣን መስሪያ ቤት አሰሪነት ተገንብተው የተመረቁት እኚሁ ፕሮጀክቶች ለሁለቱ ድልድዮች መደረሻ መንገድ ግንባታ ስራ ማስፈፀሚያን ጨምሮ ጠቅላላ…

Read More

ሚኒስቴሩ ከቻይና የገጠር ልማት ፋውንዴሽን ጋር በትብብር ለመስራት ተፈራረመ

የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ከቻይና የገጠር ልማት ፋውንዴሽን ጋር በተለያዩ መስኮች በትብብር መስራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራርሟል፡፡ ስምምነቱ በ2ኛው ምዕራፍ የትብብር ማዕቀፍ በ7 ዋና ዋና የልማት መስኮች ለችግር ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ያለመ ነው ተብሏል፡፡ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)፥ ኢትዮጵያና ቻይና በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ዘርፍ ለዓመታት የዘለቀ ግንኙነት እንዳላቸው አስታውሰዋል።…

Read More

የክልሉን ህዝብ የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ የመፍታት ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል። ርዕሰ መስተደድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

የክልሉን ህዝብ የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ የመፍታት ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተደድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ። ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ በቤንች ሸኮ ዞን የተገነቡ የአጉና እና የዳማ ወንዝ ድልድይ ግንባታ ፕሮጀክቶችን ከሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በመሆን መርቀው ከፍተዋል። በክልሉ የልማት ጥያቄዎች ለመፍታት በተሰጠው ልዩ ትኩረት በተለያዩ የክልሉ አከባቢዎች በርካታ…

Read More

በክልሉ ከ35 ሺህ በላይ ህብረተሰብ ክፍሎች በREDD+ ፕሮጀክት ተጠቃሚ መሆን መቻላቸው ተገለጸ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት አከባቢ፣ደን ፣ጥበቃና አየር ንብረት ለውጥ ቢሮ የREDD+ ፕሮጀክት የ2016 ዓ.ም ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2017 መሪ ዕቅድ ዙሪያ በሚዛን አማን ከተማ መክረዋል። በመድረኩ የክልሉ አከባቢ፣ደን፣ጥበቃና አየር ንብረት ለውጥ ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ኢንጂነር አስራት ገ/ማሪያም በክልሉ በ2016 በጀት ዓመት በሬድ ፕላስ(REDD+)ፕሮጀክት በርካታ ህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ማድረግ እንደተቻለ ተናግረዋል። በክልሉ በፕሮጀክቱ የሚሰሩ…

Read More

ሕዝብን ተጠቃሚ ለማድረግ ዕቅድን በአግባቡ መተግበር እንደሚገባ ተገለጸ

አማራ ክልልን ከነበረበት ሁኔታ የሚያሻግርና ሕዝብን ተጠቃሚ የሚያደርግ ሥራ ለመተግበር ዕቅድን በኃላፊነት መፈጸም እንደሚገባ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ አስገነዘቡ፡፡ የአማራ ክልል ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች በተገኙበት የ2016 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና የ2017 በጀት ዓመት የዕቅድ ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ነው፡፡ በመድረኩም ክልሉን በተለያየ መስክ ለማሳደግና ከ2018 እስከ 2022 ዓ.ም የሚተገበር ፍኖተ-ካርታ ተዘጋጅቶ በየደረጃው ላለው አመራር…

Read More

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የኢትዮጵያ ባንኮች ህልውናን ያስቀጠለ ነው-ጠ/ ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የኢትዮጵያ ባንኮች ህልውናን ያስቀጠለ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን በተመለከተ ትናንት በሰጡት ማብራሪያ÷ኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋን ዝግ አድርጋ መቆየቷ ለዘመናት ፈተና ውስጥ እንድትወድቅ ማድረጉን ተናግረዋል፡፡ ለአብነትም የወጪ ንግዱ የሚፈለገውን ያህል የውጭ ምንዛሬ ማስገባት ተስኖት መቆየቱን ጠቅሰው፤ የኢትዮጵያ ምርቶችም በኮንትሮባንድ እንዲወጡ ማድረጉን ነው ያነሱት፡፡ ኢትዮጵያ…

Read More