“በጎነት ለጤንነት” በሚል መሪ ቃል የ2016 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ነፃ የህክምና አገልግሎት ማስጀመሪያ ፕሮግራም በካፋ ዞን ገብረ ፃዲቅ ሻዎ አጠቃላይ ሆስፒታል ተካሂዷል።
የ2016 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ ፕሮግራሙን የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ተማም እና የካፋ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ አክሊሉ አሰፋ በይፋ አስጀምሯል። የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ ፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ተማም እንዳሉት” በጎነት ለጤንነት” በሚል መሪ ቃል ተላላፊ እና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች የነፃ ምርመራና ህክምና…
