በዳውሮ ዞን የሚገኘው የድንጋይ ከሰል ፋብሪካ ለኢንቨስትመንት በር ከፋች መሆኑ ተገለጸ

በዳውሮ ዞን ባለፈው ጥር ወር ተመርቆ ወደ ሥራ የገባው የድንጋይ ከሰል ማጠቢያ ፋብሪካ ለአካባቢው የኢንቨስትመን ፍሰት በር ከፋች መሆኑ ተገልጿል፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመረቀው የኢቲ-ማዕድን ልማት አክሲዮን ማኅበር የድንጋይ ከሰል ማጠቢያ ፋብሪካ ለበርካታ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ ዕድል መፍጠሩንም የዳውሮ ዞን ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ መምሪያ አስታውቋል። የመምሪያው ኃላፊ ኃይሌ ዱባለ የድንጋይ ከሰል ግብዓት…

Read More

የመስኖ ልማት የአየር ንብረት ተፅዕኖን ለመከላከል የጎላ ሚና እንዳለው ተጠቆመ

የመስኖ ልማት የምግብ ሉዓላዊነትን ከማረጋገጥ ባሻገር የአየር ንብረት ተፅዕኖን ለመከላከል የጎላ ሚና እንዳለው የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አማካሪ ታየ ሙሉጌታ ኢትዮጵያ ያላትን ውሃዎች በመስኖ ተጠቅማ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራች መሆኗን ተናግረዋል፡፡ በዚሁም ያላትን የውሃ ሀብት እና ሰፊ መሬት ተጠቅማ በመስኖ የምትለማ ሀገር መሆኗን አረጋግጣለችም ነው ያሉት። ከጊዜ ወደ ጊዜ…

Read More

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ የአፈጣጠር ችግር ያለባቸው ግለሰቦች በዘመቻ ነፃ የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ ከሚዲያ አመራርና ባለሙያዎች እንዲሁም ከሃይማኖት አባቶች ጋር የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ በኮንታ ዞን አመያ ከተማ አካሂዷል።

በተፈጥሮ ችግር የተወለዱ ህፃናት የነፃ ህክምና እንዲያገኙ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የድርሻውን እንዲወጣም ጥሪ ቀርቧል። በመድረኩ ላይ የተገኙት የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ተመም እንደተናገሩት በክልሉ በአፈጣጠር ችግሮች ምክንያት በማህበረሰቡ ውስጥ ተደብቀው ለማህበራዊና ለስነ ልቦናዊ ችግሮች የሚጋለጡ ማህበረሰብ ክፍሎችን በነጻ ቀዶ ህክምና ዙሪያ የሀይማኖት እና የሚዲያ ተቋማት ድርሻ ከፍተኛ መሆኑን ገልፀዋል። የችግሩ ተጠቂ የሆኑ የህብረተሰብ…

Read More

በቤንች ሸኮ ዞን የ2017 የግብርና የበልግ ሥራዎች ላይ ትኩረት ያደረገ ዉይይት ተካሄደ

በመድረኩ ላይ የቤንች ሸኮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን እንደገለፁት ዞኑ ያለውን የተፈጥሮ ሀብት በአግባቡ ለይቶ በቅንጅት በመምራት ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የህዝብ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ ከምንጊዜ በላይ መስራት ይጠበቃል ብለዋል። ፓርቲያችን ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት በ24/7 መሠረት ጊዜን በአግባቡ በመጠቀም ለምርትና ምርታማነት በቅንጅት መስራት ከሁሉም እንደሚጨበቅ አሳስበዋል። በዞኑ በአንድ አንድ የግብርና ስራዎች ላይ የተመዘገበውን የተሻለ ውጤት…

Read More

ሪፖርታዥ”

በክልሉ የአርብቶ አደሩን ኑሮ መሠረት ያደረጉ ሁሉ አቀፍ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ ናቸው፡- የክልሉ አርብቶ አደርና ቆላማ አካባቢ ጉዳይ ቢሮ የክልሉን አርብቶ አደር አካባቢ እምቅ አቅም መሠረት ያደረጉና የህብረተሰቡን የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ነው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አርብቶ አደርና ቆላማ አካባቢ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ አቶ ታምሩ ቦኒ ገልፀዋል፡፡ በክልሉ በቆላማው አካባቢ…

Read More

ብሔራዊ ጥቅም በሀገራዊ ምክክር ሂደት

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር በተመሰረበት አዋጅ 1265/2014 ላይ ብሔራዊ ጥቅም ከኮሚሽኑ መርሆዎች አንዱ ተደረጎ ተደንግጓል፡፡ እዚህ ላይ የሀገራዊ ምክክር ሂደቶች እና ተጠባቂ ውጤቶች የአንድን ሀገር ብሔራዊ ጥቅም በምን መልኩ ሊያስጠብቁ እንደሚችሉ ጥያቄ ማንሳቱ ተገቢ ነው፡፡ ሀገራት በሀገራዊ ምክክር ሂደት ውስጥ ሲያልፉ ሊያሳኩ የሚሹት በተለያዩ ባለድርሻ አካላት መካከል ያሉ መሰረታዊ የሀሳብ ልዩነቶችን በመፍታት እና ሀገራዊ መግባባትን እንዲፈጠር…

Read More

በ22 የተቋሙ አመራርና ሠራተኞች ላይ ርምጃ ተወሰደ

የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ እና ብልሹ አሠራርን ለመቅረፍ በተከናወነ ሥራ በ22 አመራርና ሠራተኞች ላይ አሥተዳደራዊ ርምጃ መውሰዱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ፡፡ ርምጃው የተወሰደው ከደንበኞች የቀረቡ የብልሹ አሠራርና ሙስና ጥቆማዎችን መሰረት በማድረግ መሆኑን ተቋሙ ለፋና ዲጂታል ገልጿል፡፡ በዚሁ መሠረት አስፈላጊው ማጣሪያ ተደርጎ ሦስቱ በጽሑፍ ማስጠንቀቂያ እና 19ኙ ደግሞ በደመወዝ ቅጣት መቀጣታቸውን ነው ያስታወቀው፡፡ በሌላ በኩል በበጀት ዓመቱ…

Read More

የዓለም አቀፍና ቀጣናዊ አጋር ድርጅቶች አመራሮች የሕዳሴ ግድብን ጎበኙ

የዓለም አቀፍ አጋር ድርጅቶችና ቀጣናዊ አጋር ድርጅቶች አመራሮች እንዲሁም የግድብ ደህንነት ባለሞያዎች የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጎብኝተዋል። በውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴዔታ አብርሃ አዱኛ (ዶ/ር) በተመራው የሕዳሴ ግድብ ጉብኝት መርሐ ግብር የተፋሰሱ ተጋሪ ሀገራት ኮሚሽነሮችና ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች ተሳትፈዋል። በተጨማሪም የካናዳና የአውስትራሊያ ግድቦች ማህበር፣ የኖርዌይ የሀይድሮፓወር ማህበር እንዲሁም የዛምቢያ ዛምቤዚ ወንዝ ባለስልጣን አመራሮች መሳተፋቸው ተገልጿል። የጉብኝት…

Read More

የዓድዋ ድል ዛሬም ለኢትዮጵያ አንድነትና እድገት በሚተጉ ልጆቿ ዳግም እየተገለጠ ነው – ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ

የዓድዋ ድል ዛሬም ለኢትዮጵያ አንድነትና እድገት በሚተጉ ልጆቿ ዳግም እየተገለጠ እንደሚገኝ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ገለጹ። 129ኛው የዓድዋ ድል በዓል በአድዋ መታሰቢያ ሙዚየም በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል። በበዓሉ በክብር እንግድነት የተገኙት ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ባስተላለፉት መልዕክት በዓሉ ለአፍሪካውያንና መላ ጥቁር ህዝቦች ተምሳሌት የሆነና የሴቶችን የፖለቲካ ጥበብ ያሳየ ነው። የዓደዋ ድል ለአፍሪካውያንና ለመላ ጥቁር ህዝቦች ተስፋንና…

Read More

የዓድዋ ድል አፍሪካ እጣ ፋንታዋን ያለማንም ጣልቃ ገብነት በራሷ መበየን እንደምትችል ያረጋገጠ ነው፦የቀድሞው የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋቂ ማህማት

የዓድዋ ድል አፍሪካ እጣ ፋንታዋን ያለማንም ጣልቃ ገብነት በራሷ መበየን እንደምትችል ያረጋገጠ ነው ሲሉ የቀድሞው የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋቂ ማህማት ገለጹ። 129ኛው የዓድዋ ድል በዓል “ዓድዋ የጥቁር ህዝቦች ድል” በሚል መሪ ሀሳብ በዓድዋ ድል መታሰቢያ በተለያዩ መርሃ ግብሮች እየተከበረ ይገኛል። የቀድሞው የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋቂ ማህማት በበዓሉ አከባበር ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት…

Read More