የክልሉን የታክስ አስተዳደርና የገቢ አሰባሰብ ስርዓት ሙሉ በሙሉ በቴክኖሎጂ የማዘመን ስራ እየተሰራ መሆኑን የገቢዎች ቢሮ አስታወቀ
የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ለ114 የገቢ ተቋም ባለሙያዎች በሲግታክስ የመረጃ ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ዙሪያ ስልጠና በሚዛን አማን ከተማ እየተሠጠ ነው። የገቢዎች ቢሮ ምክትል ኃላፊና የኦፕሬሽን ዘርፍ ኃላፊ አቶ ወንዱ ታደሰ በስልጠናው ማስጀመሪያ ላይ ተገኝተው ቢሮው የታክስ አስተዳደርና የገቢ አሰባሰብ ስርዓቱን የዘመነ ለማድግ ከዚህ ቀደም ብዙ ጥረቶችን ሲያደርግ መቆየቱን ተናግረዋል። ባለፋት ጊዜያት በሲግታክስ ተጠቅመን የግብር ግመታንና ውሳኔውን ለማውጣት…
