ብልጽግና ፓርቲ የ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ማኒፌስቶ እና የምርጫ ምልክት ማስተዋወቂያ መርሃ ግብር እየተካሄደ ነዉ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ”ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር” በሚል መሪ የ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ማኒፌስቶ እና ምርጫ ምልክት ማስተዋወቂያ መርሃ ግብር በቦንጋ ከተማ እያካሄደ ይገኛል። የፓርቲዉ ማኒፌስቶ እና የምርጫ ምልክት ማስተዋወቂያ መርሐ -ግብሩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በተገኙበት በመካሄድ ላይ ይገኛል። የብልጽግና ፓርቲ የ7ኛው ሀገራዊ የምርጫ ምልክት ”የሰንዴ…

Read More

የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የዓመታት ጉዞና ትጥቅ የሚያሳይ የፎቶ ዐውደ ርዕይ በሐዋሳ ተከፈተ

በሀገር መከላከያ ሠራዊት የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ 65ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል አካል የሆነ የዕዙን የዓመታት ጉዞና ትጥቅ የሚያሳይ የፎቶ ዐውደ-ርዕይ በሐዋሳ ከተማ ተከፍቷል። የፎቶ ዐውደ-ርዕዩን መርቀው የከፈቱት የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ናቸው። በዚሁ ዝግጅት ላይ የጦር ኃይሎች ምክትል ኤታማዦር ሹም ጄነራል አበባው ታደሰ፣ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ…

Read More

የመራጮች ምዝገባ ቁሳቁስ ዝግጅት እየተከናወነ ነው- ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚያስፈልጉ የመራጮች ምዝገባ ቁሳቁሶችን የማደራጀትና የማሰራጨት ዝግጅት እየተከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ገለጸ። ቦርዱ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ የሚያገለግሉ ቁሳቁሶችን የማዘጋጀት ሥራዎችን ለመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች አስጎብኝቷል። በዚሁ ወቅት በቦርዱ የሎጀስቲክስ ኃላፊ አቶ መላከ አሉላ፤ የመራጮች ምዝገባ ቁሳቁሶችን ለየምርጫ ጣቢያዎቹ የመለየትና የመደልደል ሥራዎች በጥንቃቄ እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል። ኢቢሲ እንደዘገበው እነዚህ ቁሳቁሶች…

Read More

ኢትዮጵያ ከቱሪዝም ዘርፉ 2.6 ቢሊዮን ብር ገቢ አገኘች

ኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ከ700 ሺህ በላይ ዓለም አቀፍ ቱሪስቶችን በማስተናገድ 2.6 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቷን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ። የቱሪዝም ዘርፉ አዳዲስ መዳረሻዎችን በመገንባትና ነባሮችን በማደስ ባሳየው ከፍተኛ መነቃቃት፣ በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት ብቻ ከ700 ሺህ በላይ ጎብኚዎችን መሳብ ችሏል። ይህ አፈጻጸም ለሀገሪቱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ግኝት አስተዋጽኦ ያበረከተ ሲሆን፣ ለውጤቱ መገኘት…

Read More

ከ18ሺህ ለሚልቁ የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ተሰጠ

በተያዘው በጀት ዓመት ስድስት ወራት ከ18ሺህ ለሚልቁ የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታወቀ። የመደመር መንግሥት ኢትዮጵያን ተመራጭ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ለማድረግ መሰረተ ልማት ከማሟላት ባለፈ የሚያሰራ የህግ ማዕቀፎችን በማዘጋጀት ለባለሃብቶች ምቹ ከባቢን ፈጥሯል። የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር ዳጋቶ ኩምቤ እንደገለጹት ኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች መሰማራት ለሚፈልጉ ባለሀብቶች ተመራጭ መዳረሻ ሆናለች። የመደመር መንግሥት በዘርፉ…

Read More

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተግባራትና ኃላፊነቶች

ምርጫ ቦርድ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ህገ መንግሥት አንቀጽ 102 መሠረት የተቋቋመ ገለልተኛ ህገ መንግሥታዊ ተቋም ነው። ቦርዱ ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ የፌዴራል እና የክልል ጽህፈት ቤቶችን ያደራጀ ሲሆን በሁሉም ክልልሎች እና ከተማ መስተዳድሮች እንዲሁም በፌደራል ደረጃ ቢሮዎች አሉት። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ስድስት ሀገራዊ ምርጫ ያስፈጸመ ሲሆን ከዚህም በተጨማሪ አራት የአካባቢ ምርጫ፣ እና ስምንት ሕዝበ ውሳኔዎችን…

Read More

vhgm

በኢትዮጵያ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት የደቡብ ማዕከል ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የአዴይ ፕሮግራም ስትሪንግና ቴክኒካል ኮሚቴ አባላት የጋራ መድረክ በታርጫ ከተማ ተካሂዷል። በውይይት መድረኩ የተገኙ የክልሉ ስራና ክህሎት ቢሮ ሀላፊና የ”አደይ” ፕሮግራም የስትሪንግና ቴክኒክ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ዶ/ር ዐብይ አንዴሞ የአዴይ ፕሮግራም በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በፕሮግራሙ በታቀፉ ዞኖች 4078 ስራ አጥ ወጣቶችን ተጠቃሚ…

Read More

የሶርጋ ኢኮ ሎጅ ግንባታ በቅርቡ ይጠናቀቃል፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

የሶርጋ ኢኮ ሎጅ ግንባታ ሥራ በፍጥነት እየተከናወነ ሲሆን በቅርቡ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባስተላለፉት መልዕክት፣ በሶርጋ ሐይቅ ላይ የሚገኘው የሶርጋ ኢኮ ሎጅ በአሁኑ ወቅት በ14 ሄክታር መሬት ላይ እየተገነባ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። ከነቀምቴ ከተማ በ6 ኪሎ ሜትሮች ርቀት ላይ ብቻ የሚገኘው የሶርጋ ኢኮ ሎጅ አካባቢውን ከመጠበቅ ባሻገር በኮንስትራክሽን…

Read More

ሴቶች ለሀገር ግንባታና ለብልጽግና ጉዞ ያላቸው ሚና የማይተካ ነው ፦አቶ አለማየሁ አለሙ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ አስተባባሪነት ክልላዊ የንቅናቄ ማጠቃለያ መድረክ በቴፒ እየተካሄደ ይገኛል። መድረኩ “በሴቶች ተሳትፎ የጸናችና የበለጸገች ኢትዮጵያ” በሚል መሪ ቃል በየደረጃው ከሚገኙ ሴቶች ጋር በተካሄዱ የንቅናቄ ሥራዎች ላይ ግምገማ ለማድረግና ለቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ለመወሰን የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል። በመድረኩ ላይ የተገኙት የሸካ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ…

Read More

ባለፉት የለውጥ ዓመታት የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በተደረገው ጥረት በርካታ ውጤቶች ተመዝግበዋል፦ ፈለቀች ተክለማሪየም (ዶ/ር)

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዞቦች ክልል ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ቅ/ጽ/ቤት አስተባባሪነት በሴቶች ተሳትፎ የፀናችና የበለፀገች ኢትዮጵያ” በሚል መሪ ሀሳብ በቦንጋ ከተማ ክልላዊ ማጠቃለያ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል። በመድረኩ የተገኙት የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ስራ አስፈጻሚና የማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል ፕላን ቢሮ ምክትል ኃላፊ (ዶ/ር )ፈለቀች ተክለማርያም እንዳሉት ባለፋት የለውጥ ዓመታት ሴቶችን ማኅበራዊ፤ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ገፅታ የቀየረ ዕምርታዊ…

Read More