የመራጮች ምዝገባ ቁሳቁስ ዝግጅት እየተከናወነ ነው- ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚያስፈልጉ የመራጮች ምዝገባ ቁሳቁሶችን የማደራጀትና የማሰራጨት ዝግጅት እየተከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ገለጸ። ቦርዱ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ የሚያገለግሉ ቁሳቁሶችን የማዘጋጀት ሥራዎችን ለመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች አስጎብኝቷል። በዚሁ ወቅት በቦርዱ የሎጀስቲክስ ኃላፊ አቶ መላከ አሉላ፤ የመራጮች ምዝገባ ቁሳቁሶችን ለየምርጫ ጣቢያዎቹ የመለየትና የመደልደል ሥራዎች በጥንቃቄ እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል። ኢቢሲ እንደዘገበው እነዚህ ቁሳቁሶች…

Read More

ኢትዮጵያ ከቱሪዝም ዘርፉ 2.6 ቢሊዮን ብር ገቢ አገኘች

ኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ከ700 ሺህ በላይ ዓለም አቀፍ ቱሪስቶችን በማስተናገድ 2.6 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቷን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ። የቱሪዝም ዘርፉ አዳዲስ መዳረሻዎችን በመገንባትና ነባሮችን በማደስ ባሳየው ከፍተኛ መነቃቃት፣ በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት ብቻ ከ700 ሺህ በላይ ጎብኚዎችን መሳብ ችሏል። ይህ አፈጻጸም ለሀገሪቱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ግኝት አስተዋጽኦ ያበረከተ ሲሆን፣ ለውጤቱ መገኘት…

Read More

ከ18ሺህ ለሚልቁ የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ተሰጠ

በተያዘው በጀት ዓመት ስድስት ወራት ከ18ሺህ ለሚልቁ የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታወቀ። የመደመር መንግሥት ኢትዮጵያን ተመራጭ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ለማድረግ መሰረተ ልማት ከማሟላት ባለፈ የሚያሰራ የህግ ማዕቀፎችን በማዘጋጀት ለባለሃብቶች ምቹ ከባቢን ፈጥሯል። የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር ዳጋቶ ኩምቤ እንደገለጹት ኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች መሰማራት ለሚፈልጉ ባለሀብቶች ተመራጭ መዳረሻ ሆናለች። የመደመር መንግሥት በዘርፉ…

Read More

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተግባራትና ኃላፊነቶች

ምርጫ ቦርድ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ህገ መንግሥት አንቀጽ 102 መሠረት የተቋቋመ ገለልተኛ ህገ መንግሥታዊ ተቋም ነው። ቦርዱ ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ የፌዴራል እና የክልል ጽህፈት ቤቶችን ያደራጀ ሲሆን በሁሉም ክልልሎች እና ከተማ መስተዳድሮች እንዲሁም በፌደራል ደረጃ ቢሮዎች አሉት። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ስድስት ሀገራዊ ምርጫ ያስፈጸመ ሲሆን ከዚህም በተጨማሪ አራት የአካባቢ ምርጫ፣ እና ስምንት ሕዝበ ውሳኔዎችን…

Read More

የሶርጋ ኢኮ ሎጅ ግንባታ በቅርቡ ይጠናቀቃል፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

የሶርጋ ኢኮ ሎጅ ግንባታ ሥራ በፍጥነት እየተከናወነ ሲሆን በቅርቡ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባስተላለፉት መልዕክት፣ በሶርጋ ሐይቅ ላይ የሚገኘው የሶርጋ ኢኮ ሎጅ በአሁኑ ወቅት በ14 ሄክታር መሬት ላይ እየተገነባ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። ከነቀምቴ ከተማ በ6 ኪሎ ሜትሮች ርቀት ላይ ብቻ የሚገኘው የሶርጋ ኢኮ ሎጅ አካባቢውን ከመጠበቅ ባሻገር በኮንስትራክሽን…

Read More

89ኛው የየካቲት 12 ሰማዕታት መታሰቢያ በዓል ተከበረ

የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር 89ኛውን የየካቲት 12 ሰማዕታት መታሰቢያ በዓል በስድስት ኪሎ በሚገኘው የሰማዕታት መታሰቢያ ሐውልት ፊት ለፊት አክብሯል። በበዓሉ ላይ አባትና እናት አርበኞች በመገኘት የአበባ ጉንጉን በማኖር የሰማዕታቱን መስዋዕትነት ዘክረዋል። የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር ፕሬዝዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን፤ ወጣቱ ትውልድ አያትና ቅድመ አያቶቹ ለሀገር ፍቅርና ለአንድነት የከፈሉትን የሕይወት መስዋዕትነት በማሰብ፣ ሀገሩን…

Read More

“‎ዛሬ በቄለም ወለጋ ዞን ሃዋ ገላን ወረዳ በሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብር የለማ የሙዝ እርሻ ከባቢን ጎብኝቻለሁ።‎

አርሶአደሮች በፍጹም ጽናት፣ ቅንጅት እና ትብብር አካባቢያቸውን በቀየረ ስራ በመመልከቴ ደስ ብሎኛል። የተመለከትነው የእርሻ ስራ፤ የአካባቢ መሬትን እና የውኃ ኃብትን በአግባቡ መጠቀም ከተቻለ ትርጉም ያለው ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ማሳያ ነው። ባህላዊ የመስኖ ዘዴዎችን በመጠቀም እና በቅርብ ያለ ኃብትን በሚገባ ጥቅም ላይ በማዋል ማኅበረሰቡ ውጤታማ እና ተስፋ ሰጪ የግብርና ማዕከል መፍጠር ችሏል። በተለይም የመንገድ መሠረተ ልማት…

Read More

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሐዊ እና ገለልተኛ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ዳኞች ሚናቸውን በአግባቡ ሊወጡ ይገባል – የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሐዊ እና ገለልተኛ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ዳኞች ሚናቸውን በአግባቡ ሊወጡ ይገባል ሲሉ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ አሳስበዋል። የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከምርጫ ቦርድ ጋር በመተባበር ከምርጫ ጉዳዮች ጋር በተያያዙ በሚመጡ ቅሬታዎች የአፈታት ዘዴ ላይ ለፌደራል እና ለክልል ዳኞች ስልጠና እየሰጠ ነው። ምርጫው ነፃ እና ገለልተኛ እንዲሆን ተቋማዊ…

Read More

ኢትዮጵያ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዘርፉን የምትገነባ እና የምትመራ እንድትሆን ለማድረግ እየተሰራ ነው – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

ኢትዮጵያ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዘመን ተመልካች ብቻ ሳትሆን ዘርፉን የምትገነባ እና የምትመራ እንድትሆን ለማድረግ እየተሰራ ነው አሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዛሬው ዕለት የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዩኒቨርሲቲ ፖድ (Al UniPod) የፈጠራ ማዕከልን ስራ አስጀምረዋል። ኢትዮጵያ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዘመን ተመልካች ብቻ ሳትሆን ዘርፉን የምትገነባ፣ አስተዋጽኦ የምታበረክትና የምትመራ እንዲሁም ወደፊት ለመራመድ አዲስ ምዕራፍ የምትከፍትበት መሆኑን…

Read More

ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን በሚያስከብሩ ጉዳዮች ላይ በንቃት እንደምትሳተፍ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ

ኢትዮጵያ በአፍሪካ ሕብረት ጉባኤ እና በጣሊያን-አፍሪካ ጉባኤ ላይ ብሔራዊ ጥቅሞቿን በሚያስጠብቁና ከፍ በሚያደርጉ ጉዳዮች ላይ በንቃት ለመሳተፍ መዘጋጀቷን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ። የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ በሰጡት መግለጫ እንዳመለከቱት፣ በአዲስ አበባ በሚካሄዱት ጉባኤዎች የሀገራት መሪዎች፣ ሚኒስትሮችና፣ ከፍተኛ ዲፕሎማቶችን ጨምሮ በርካታ ቁጥር ያላቸው እንግዶች ይታደማሉ። ኢትዮጵያም ይህንን አጋጣሚ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስከበርና ተሰሚነቷን…

Read More