የሰላማችን ፈተናዎች እና የታሪክ ጠባሳዎች፦ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ማብራሪያ
ኢትዮጵያ በዘላቂ ሰላም እንዳትኖር እንቅፋት የሆኑባትን መሠረታዊ ምክንያቶች ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ በምክር ቤት ባደረጉት ንግግር በዝርዝር አብራርተዋል። እንደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለፃ፣ ለሰላም እጦት ቀዳሚው ምክንያት ልዩነቶችን በኃይል ብቻ የመፍታት ከጥንት ጀምሮ የቆየው የተሳሳተ ልምምድ ነው ብለዋል። ይህ ባህል ለውይይትና ለሰላማዊ መፍትሄዎች ዕድል በመንፈግ ሀገርን በግጭት አዙሪት ውስጥ እንድትቆይ አድርጓታል ነው ያሉት። በሁለተኛ…
