“በሀገሩ ሉዓላዊነት የማይደራደር ሠራዊት ማፍራት ተጠናክሮ ይቀጥላል”- ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
ወቅቱን የሚመጥን ሠራዊት የማፍራት ተልዕኮ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ተናገሩ። ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ አየር ኃይል ላስመረቃቸው እጩ መኮንኖች ማዕረግ የማልበስ ሥነ-ሥርዓት አከናውነዋል። በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግርም፣ “ኢትዮጵያ ቀደምት ሀገር በመሆኗ እና ካላት የጂኦ-ፓለቲካ አቀማመጥ አንጻር ጠላት ተደጋጋሚ ትንኮሳ ቢያደርግባትም ጀግኖች አርበኞች የተከበረች ሀገርን አስረክበውናል” ብለዋል። በዘመናዊ…
