Trendings

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ዘርፍ ኢትዮጵያ እያስመዘገበችው ላለው ፈጣን እድገት ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው፦ሚኒስትር አለሙ ስሜ(ዶ/ር)

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ዘርፍ ኢትዮጵያ እያስመዘገበችው ላለው ፈጣን እድገት ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ(ዶ/ር) ገለጹ። የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ዘርፍ የ2017 በጀት አመት ዘጠኝ ወራት አፈጻጸም ሀገር አቀፍ የሴክተር ጉባኤ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ(ዶ/ር) እንዲሁም የፌደራል እና የክልል የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ዘርፍ አመራሮች ተገኝተዋል። ሚኒስትር አለሙ…

Read More

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ በትውልድ ቅብብሎሽ የተገነባ ኅብረብሔራዊ ሠራዊት ነው፦አፈ-ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ በትውልድ ቅብብሎሽ የተገነባ ኅብረብሔራዊ ሠራዊትና ተቋም መሆኑን የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር ገለጹ። ሀገር አቀፍ 116ኛው የኢትዮጵያ ፖሊስ ቀን የሲምፖዚየም እና አውደ-ርዕይ ዝግጅት “የተለወጠ ፖሊስ፥ እየተለወጠ ላለ ሀገር” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ ሳይንስ ሙዚየም መከበር ጀምሯል። የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፥ የኢትዮጵያ ፖሊስ…

Read More

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በ6 ጉዳዮች ላይ ውሳኔ አሳለፈ

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 44ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል፡፡ 1. ምክር ቤቱ በቅድሚያ የተወያየው ከጣሊያን ሪፐብሊክ መንግሥት እና ከዓለም አቀፍ የልማት ማህበር ጋር በተፈረሙ ሁለት የፋይናንስ ድጋፍ ስምምነቶች ላይ ነው፡፡ ከጣሊያን ሪፐብሊክ መንግስት የተገኘው የ11,500,000 ዩሮ ለአካባቢያዊና አረንጓዴ ኢኮኖሚ ልማት የበጀት ድጋፍ ፕሮግራም ማስፈፀሚያ የሚውል ሲሆን የ16 ዓመት የችሮታ…

Read More

“ፈጠራና ፍጥነት የታከለበት የክህሎት ግንባታ ቀጣይነት ላለው የሥራ እድል ፈጠራና ዋስትና ወሳኝ ነው።”

እንኳን ለዓለም የሠራተኞች ቀን በሰላም አደረሳችሁ! ሀገራችን “በአምራች ኢንዱስትሪዎችና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ምቹ የሥራ ሁኔታ ለማህበራዊ ፍትህ” በሚል መሪ ቃል በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ136ኛ በሀገራችን ደግሞ ለ50ኛ ጊዜ የሚከበረውን የዓለም አቀፍ ሠራተኞች በዓል እያከበረች ትገኛለች። ኢትዮጵያ የዓለም የሠራተኞች ቀንን የምታከብረው የኢንዱስትሪ ሰላምን፣ የሥራ ላይ ደኅንነትንና የሠራተኞችን ክሕሎት ማሳደግን ልዩ ትኩረት በመስጠት ነው፡፡ ወደ ብልጽግና የሚደረገዉ…

Read More

መምህራንን አቅም በመገንባት የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው – ብርሀኑ ነጋ (ፕ/ር)

ኢትዮጵያ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ በማሻሻል እና የመምህራንን አቅም በመገንባት የትምህርት ጥራትን ማረጋገጥ የሚያስችል እንቅስቃሴ እያደረገች መሆኑን የትምህርት ሚኒስትር ብርሀኑ ነጋ (ፕ/ር) ገለጹ። የትምህርት ሚኒስቴር፣ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከአፍሪካን ብሬይን ጋር በመተባበር ያዘጋጁት ‘በ21ኛው ክፍለ ዘመን አፍሪካን ማስተማርና ማብቃት’ በሚል መሪ ሃሳብ ለሶስት ቀናት የተካሄደው ኢኖቬሽን አፍሪካ 2025 ጉባኤ ዛሬ ተጠናቋል። በዚህ…

Read More

የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ በመጪው ቅዳሜ በይፋ ይከፈታል

የ2017 ዓ-ም ኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ በመጪው ቅዳሜ በአዲስ አበባ በይፋ እንደሚከፈት የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ። የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ኤክስፖውን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ኢንዱስትሪዎች ያጋጥማቸው የነበሩ ችግሮች ደረጃ በደረጃ እንዲፈቱና የማምረት አቅማቸው እንዲጎለብት ማድረጉን አንስተዋል። ንቅናቄው የአገር ውስጥ ምርት አጠቃቀም ላይ ሰፊ ለውጦች መምጣታቸውን ገልጸዋል። 3ኛው የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ በመጪው ቅዳሜ ሚያዝያ…

Read More

ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅትን በአባልነት እንድትቀላቀል አሜሪካ ድጋፍ ታደርጋለች፦የአሜሪካ የንግድ ፅ/ቤት

ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅትን በአባልነት እንድትቀላቀል አሜሪካ ድጋፍ እንደምታደርግ ገለጸች። ከ2025 የዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋም እና የዓለም ባንክ የጸደይ ስብሰባዎች ጎን ለጎን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) በአሜሪካ የንግድ ፅ/ቤት የዓለም ንግድ ድርጅት እና የባለብዙ ወገን ጉዳዮች ረዳት ተወካይ ከሆኑት ኒል ጄ ቤክ ጋር ተወያይተዋል። በውይይቱ ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅትን በአባልነት ለመቀላቀል እያደረገች ያለውን…

Read More

የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመንግስትን የአገልግሎት አሰጣጥ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ገለጹ

የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴን ጨምሮ የተለያዩ አገራት አምባሳደሮች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫን ጎብኝተዋል። መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከል በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተመርቆ ወደ ስራ መግባቱ ይታወሳል። ማዕከሉ 12 ተቋማትን እና ከ41 በላይ አገልግሎትን በአንድ ህንፃ ማግኘት የሚያስችል ነው። የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ እንዲሁም የተለያዩ አገራት አምባሳደሮች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫን…

Read More

ኢትዮጵያና የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ በልማት ትብብር ላይ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ተስማሙ

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ ከአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ ምክትል ፕሬዝዳንት አምበሮይስ ፋዮሌ ጋር በልማትና ኢንቨስትመንት ትብብር ዙሪያ ውይይት አካሂደዋል። የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እና ማህበራዊ እድገት ዙሪያ ተጨባጭ አስተዋጽኦ ከማበርከት አኳያ ጉልህ ሚና ያላቸው ዘርፎች ላይ ለሚያደርገው ቀጣይነት ያለው ድጋፍ አቶ አህመድ ሺዴ ምስጋና አቅርበዋል። በተለይም በአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ፋይናንስ፣ ውሃ፣ የንጽህና አጠባበቅና እና…

Read More

መንግስት በፈጠራና ክህሎት ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

የትምህርት፣ የቴክኖሎጂና የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ከ’ African Brains’ ጋር በመተባበር ያዘጋጁት ኢኖቬሽን አፍሪካ 2025 ጉባኤ በአዲስ አበባ ስካይ ላይት ሆቴል መካሄድ ጀምሯል። በጉባኤው የትምህርት፣ የቴክኖሎጂና ክህሎት ጉባኤ ላይ የአፍሪካ ሀገራት የዘርፉ ሚኒስትሮችና ልዑካን ቡድን አባላት፣ የተለያዩ ዓለም አቀፍ የትምህርት አጋር ድርጅቶች፣ የግሉ ሴክተር ኢንቨስተሮች እየተሳተፉ ይገኛል። ጉባኤውን በንግግር የከፈቱት የኢፌዲሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር…

Read More