3ኛው ዓለም አቀፍ የሰላም፣ የአብሮነትና የልማት ጉባኤ መካሄድ ጀመረ
ዛሬ እና ነገ በአዲስ አበባ ከተማ የሚካሄደው 3ኛው ዓለም አቀፍ የሰላም፣ የአብሮነትና የልማት ጉባኤ መካሄድ ጀመረ። ጉባኤው በዋናነት የአፍሪካ የእምነት ማህበረሰብ ዘላቂ የልማት ግቦች ስኬትን ማፋጠን፣ የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ለማሳካት እና የአፍሪካ የ2025 የቡድን 20 ሂደት መሳካትን ትኩረት አድርጎ ነው እየተካሄደ የሚገኘው። በጉባኤው ላይ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ፣ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሃሙድ አሊ…
