Trendings

ሰላምን በተመለከተ

መንግስት ለትችት ክፍት ነው። በሚያነሳው ሃሳብ ምክንያት የታሰረ አንድም ሰው የለም። ነገር ግን በአንድ እጅ ሰላማዊ ትግል፤ በሌላ እጅ በጦርነት መንግስት ለመጣል የሚሞክሩ ኃይሎች አሉ። ይህ ህግን መጣስ ነው። ነጻነትን በአግባቡ የማስተዳደር ችግር አለ። ነገር ግን መንግስት አሁንም ለሰላም ጽኑ አቋም አለው። ችግሮች በድርድር እንዲፈቱ ነው የምንሻው። ባለፉት 7 ዓመታት ከየትኛውም የጎረቤት ሀገራት ጋር ጦርነት…

Read More

ህዳሴ ግድብን በተመለከተ

“ህዳሴ ግድብን ለመጨረስ በርካታ ችግሮች ታልፈዋል። በሚቀጥለው ዓመት መጀመሪያ አካባቢ በጋራ ሪቫን በመቁረጥ ታሪክ እናደርገዋለን። ግድቡ ለታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ጭምር ፋይዳው የጎላ ነው። ግድቡ በመሞላቱ ምክንያት አሰዋን ግድብ ላይ የጎደለ ውሃ የለም። እኛም ቃል የገባነው ይህ እንዲፈጸም ነበር። ይህም በተግባር ተሳክቷል። ግድቡ የአፍሪካ ኩራት ነው። ኢትዮጵያ መቻልን ያሳየችበት፤ ስህተታችንን ያረምንበትም ጭምር ነው።”

Read More

ፕሪቶሪያ ስምምነትን በተመለከተ

“የፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረተ ልማቶችን በመመለስ የትግራይ ህዝብ አገልግሎት እንዲያገኝ አድርጓል። ያም ሆኖ አሁንም በበቂ ሁኔታ ያልተፈጸሙ ጉዳዮች አሉ። ከዚህም አንደኛው የታጣቂዎች ተሃድሶ (ዲዲአር) ስራ ነው። ይህ በዋናነት የሚጎዳው የትግራይ ህዝብን ነው። ወጣቶች በታጣቂ ስም ከመቀመጥ ወደ ልማት መሰማራት አለባቸው። በየወሩ ለልማት መዋል የነበረበት በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ለዚህ ስራ ይወጣል። ተፈናቃዮችን ወደ ቀያቸው በመመለስ ረገድም በራያና…

Read More

በትግራይ ክልል ጦርነት አያዋጣም፦ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ተገኝተው ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በትግራይ ክልል አሁንም ወደሰላም መሄድ ይገባል ብለዋል። የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ተጨማሪ ውጊያ እንዳይነሳ የሚደነቅ ስራ ሰርቷል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ምርጫ እስኪደረግ ክልሉን ለአንድ ዓመት ያስተዳድራልም ብለዋል። በፕሪቶሪያ ስምምነት መሰረት ሙሉ ለሙሉ ያልተፈፀመው የትጥቅ ማስፈታት እና መልሶ የማቋቋም ሒደት…

Read More

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢንዱስትሪ ዘርፍን በተመለከተ የሰጡት ምላሽና ማብራሪያ:-

በኢንዱስትሪው ዘርፍ የነበረውን የውጭ ምንዛሬ አቅርቦት ችግር ለመቅረፍ መንግስት ጣልቃ በመግባት የኢኮኖሚ መሻሻያ አድርጓል፤ በዚህም ተጨባጭ ውጤት ተገኝቷል፣ የሀይል አቅርቦት ችግርን ለመቅረፍ በተከናወኑ ተግባራት በዘርፍ ኢነርጂ 100 ፐርሰንት ተደራሽ ማድረግ ተችሏል፣ ከአምናው ጋር ሲነፃፀር በኢንዱስትሪው ዘርፍ 50 በመቶ የሀይል አቅርቦት ጭማሪ ተደርጓል፣ ከግብዓት ጋር እንዲሁም ከኢንዱስትሪ መሬት አቅርቦት ጋር በተያያዘ መንግስት በርካታ ስራዎችን አከናውኗል፣ ኢትዮጵያ…

Read More