Trendings

ዘመኑ በመረጃ ብዛትና ፍጥነት የተወሳሰበ በመሆኑ በሚድያ የሚሰራጩ መረጃዎችን ጥቅምና ጉዳት ለይተን በኃለፊነት ሊንጠቀም ይገባል፦ የስልጠና ተሳታፊዎች

“የድህረ እውነት ዘመንን በእውነትና በእውቀት” በሚል መሪ ቃል በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አመራሮች፣ ለህዝብ ግንኙነትና ሚድያ ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና በቦንጋ ከተማ መሠጠቱን ቀጥሏል። ስልጠናው የድህረ እውነት ዘመንን በአግባቡ ለመረዳት የሚያስችል በቂ ግንዛቤ የተጨበጠበት እና በሚድያ ዘርፍ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ለቀጣዩ በማረም እንዴት ማህበራዊ ሚድያን ለ ገንቢ ዓላማ መጠቀም እንዳለበት የሚረዳ ነው። ከተሳታፊዎች ውስጥ ያነጋገርናቸው…

Read More

የቴፒ-ሚዛን የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክትን በሚቀጥለው በጀት ዓመት ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ ነው

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግንባታው በመካሄድ ላይ የሚገኘው እና የቤንች ሸኮን እና የሸካ ዞኖችን የሚያገናኝ የቴፒ-ሚዛን 47.87 ኪሎ ሜትር አስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክትን በቀጣዩ በጀት ዓመት ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡ በእስካሁኑ የፕሮጀክቱ አፈጻጸም የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት ፣ የማፋሰሻ ፣ የስትራክቸር ፣ የሰብ ቤዝ እና የቤዝ ኮርስ ንጣፍ እንዲሁም 25 ኪሎ ሜትር የአስፋልት…

Read More

በግብርና ምርት ዘርፍ የተሰጠው የደላላነት ፈቃድ ተሰረዘ

በግብርና ምርቶች ዘርፍ የተሰጠው የደላላነት ፈቃድ ሙሉ በሙሉ ተሰርዟል አለ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር፡፡ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴዔታ አብዱልሃኪም ሙሉ (ዶ/ር) ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንዳሉት ÷ በዘርፉ ምንም አይነት እሴት ሳይጨምሩ የንግድ ሥርዓቱን የሚረብሹ በርካታ ደላላዎች አሉ፡፡ ስለሆነም በእህል ምርት፣ በአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም በቁም እንስሳት ዘርፍ የተሰጠው የደላላነት ፈቃድ ሙሉ በሙሉ መሰረዙን ተናግረዋል፡፡ ይህን…

Read More

በመኧን ማህበረሰብና በኮንታ ኮይሻ ነዋሪዎች መካካል የተደረገው እርቀ ሰላም የነበረውን ጥላቻ በማስወገድ የእርስ በእርስ መስተጋብሮችን ይበልጥ ለማጠናከር ፋይዳው የላቀ መሆኑንም ነዋሪዎቹ ተናግረዋል ፡፡

ነዋሪዎቹ እርቀ ሰላሙ ዘላቂ እንዲሆንም የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡም ተናግረዋል ፡፡ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በመኧን ማህበረሰብና በኮንታ ኮይሻ ነዋሪዎች መካካል ለዘመናት ዘልቆ የነበረው ችግር በእርቀ ሰላምና በይቅርታ ተፈትቷል ፡፡ በነበረው የይቅርታና እርቀ ሰላም ስነ ስርዓት ከሁለቱም ወገኖች በኩል የሀገር ሽማግሌዎች፣ሀይማኖት አባቶች፣የጎሳ መሪዎችና ባላባቶች እንዲሁም የክልልና የዞን ፣የወረዳ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ስነ ስርዓቱ ተከናውኗል…

Read More

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልልን ምን ያህል ያውቃሉ?

እንደምን ቆያችሁን ውድ አምባቢዎቻችን? ባለፉት ተከታታይ ወራት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልልን ምን ያህል ያውቃሉ? በሚል አምዳችን የዞኖቻችንን ጠቀለል ያለ እይታ በወፍ በረር ማስቃኘታችን ይታወቃል። ከእነዚህም: ስለ ካፋ ዞን ባስቃኘናችሁ ክፍል: በካፋ ዞን ውስጥ የሚገኙ ታሪካዊ፣ ተፈጥሮአዊና የቱሪስት በዳረሻዎችን እንድሁም በዞኑ ውስጥ ከሚገኙ ነባር ብሔረሰቦች ውስጥ አንዱ የሆነውን ካፈቾ የሚታወቁባቸውን ባህላዊ እሴቶች ጠቅሰናችሁ ነበር። ዛሬ…

Read More

ወቅታዊ፣ ትክክለኛና ግልፅ መረጃ በፍጥነትና በአስተማማኝ ሁኔታ በመስጠት ቀውስን መቀነስ እንደሚገባ ተገለጸ

የድህረ እውነት ዘመንን በእውነትና በዕውቀት” በሚል መሪ ቃል ለደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል፤ ለህዝብ ግንኙነትና ሚዲያ ባለሙያዎችና አመራሮች በቦንጋ ከተማ እየተሰጠ ያለው የአቅም ግንባታ ስልጠና እየቀጠለ ይገኛል። የቀውስ ጊዜ ኮሙኒኬሽን እና የመረጃ ማጣራት ሂደት ላይ የስልጠና ሰነድ በኢዜአ የሚዲያ ክትትልና መረጃ ማጣራት ዳይረክቶረት ዳይሬክተር በሆኑት አቶ አብዱ አሊ ለተሳታፊዎች እየቀረበ ይገኛል። ቀውስ በተፈጥሮም ሆነ በሰው…

Read More

ችግሮች በተከሰቱባቸው አካባቢዎች ዘላቂ ሰላም እንዲረጋገጥ የሀገር ሽማግሌዎችና የጎሳ መሪዎች ትኩረት እንዲሰጡ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ አሳሰቡ።

የመኧን አርብቶ አደር ማህበረሰብ ከኮንታና አጎራባች ህዝቦች ጋር የይቅርታና የእርቅ ስነ ስርዓት በኮይሻ ከተማ ተካሂዷል ። በህብረተሰቡ ዘንድ ዘልቆ የቆየውን ተቃርኖ ለመፍታት በመኧን ማህበረሰብ ባህላዊ የእርቅና የይቅርታ ስነስርዓት (ታራይ) በመፈጸም ተከናውኗል ። የእርቅና የይቅርታ ስነስርዓቱ ላይ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ በመኧንና ኮንታ ኮይሻ ህብረተሰብ ዘንድ የቆየውን ቁርሾ ለመቅረፍ የክልሉ መንግስት ብርቱ…

Read More

ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ኦዲት ግኝት አስመላሽ ግብረ-ሀይል በኦዲት ያገኛቸዉን ግኝቶች እና ተቋማት የሰጡት ምላሽ ላይ የግምገማ መድረክ በቦንጋ ከተማ እያካሄዱ ነው።

የኦዲት ግኝት አስመላሽ ግብረ-ኃይል በአምስት ዞኖች ላይ በኦዲት ያገኛቸዉን ግኝቶችና ተቋማት የሰጡት ምላሽ ላይ የግምገማና የማስተካከያ ውይይት እያደረገ ይገኛል። በቦንጋ ክላስተር ላይ ያሉ የክልል ተቋማት፣ በዞኑ ዉስጥ የሚገኙ ወረዳዎችና የዞኑ ፋይናንስን የሚመለከት የኦዲት ግኝት መሆኑም ተመላክቷል። የክልል ግብርና ቢሮ፣የቦንጋ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ፣የቦንጋ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ፣ገብረ ጻዲቅ ሻዎ አጠቃላይ ሆስፒታል፣ የካፋ ዞን ፋይናንስ መምሪያ፣የገዋታ ወረዳ…

Read More

የጠቅላይ ሚኒስትር ኢንሸቲቮች ለአገር ኢኮኖሚ ዕድገት የበኩላቸውን ድርሻ እየተወጡ እንደሚገኙ ተገለጸ

ለአንድ አገረ መንግሥት ግንባታ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተቀናጅተው መሥራት ወሳኝ መሆኑ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባላት ገለጹ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች አባላት የንጉሥ ሃላላ ሎጅና ሌሎች ታሪካዊ ቦታዎችንና ቅርሶችን ለመጎብኘት ወደ ዳዉሮ ዞን ገብተዋል። የንጉሥ ሃላላ የድንጋይ ካቦችን፣ የጊቤ III ሃይድሮ ኤሌክትሪክ የኃይል ማመንጫ የሰው ሰራሽ ሐይቅና በጠቅላይ ሚኒስትር ሃሳብ አመንጪነት የተገነባው የሃላላ ሎጅና ሙዚየም…

Read More

በጨና ወረዳ ሻቻ ቀበሌ ከ19 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው የጪታ አነስተኛ ድልድይ ተመረቀ።

በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ብልጽግና ፓርቲ ቅርጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን፣ የክልሉ ረዳት የመንግስት ተጠሪ እና አደረጃጀት ዘርፍ ሃላፊ አቶ በላይ ተሰማን ጨምሮ የክልል የዞንና የወረዳ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል። የአካባቢው ማህበረሰብ ከዚህ ቀደም በወንዝ ሙላት ሲቸገር እንደነበር የተገለጸ ሲሆን የአነስተኛ ድልድይ መገንባት ይህን ችግር የሚያቀል ይሆናል…

Read More