Trendings

የመንግስት ተቋማትን የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትና ቅልጥፍናን ለማሳደግ የሚያስችል የሪፎርም ትግበራትን እያከናወነ እንደሚገኝ የክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስና ሰዉ ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ፐብሊክ ሰርቪስና ሰዉ ሀብት ልማት ቢሮ በሪፎርም የሚካተቱ የክልል ቢሮዎች፣ ለዞን መምሪያ ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች በመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ፖሊሲና በክልሉ ፍኖተ ካርታ ላይ የተዘጋጀ ስልጠና በቦንጋ ከተማ እተሰጠ ይገኛል፡፡ የቢሮዉ ሃላፊ አቶ አስራት አዳሮ በእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግራቸዉ፣የመንግስት የአገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም ትግበራ ዓላማ የመንግስት ተቋማትን ቅልጥፍናና ዉጤታማነት፣ግልጽነት፣እና ተጠያቂነት በማሻሻል ቀልጣፋ ዉጤታማ…

Read More

በክልሉ ከ2.4 ሚሊዮን በላይ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ለማከናወን የቅድመ ዝግጅት ሥራ መጠናቀቁ ተገለጸ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ በበጎ ፈቃድ ስታንዳርድ እና ትመና ላይ ለዞን አመራሮች እና ባለሙያዎች ስልጠና በቦንጋ ከተማ እየሰጠ ይገኛል። በዘንድሮው የክረምት ወጣቶች በጎ ፍቃድ አግልግሎት ከ2.4 ሚሊዮን በላይ የኅብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ የሚያደርግ የበጎ ፍቃድ አግልግሎት ለማከናወን የቅድመ ዝግጅት ሥራ መጠናቀቁን ነው የክልሉ የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ…

Read More

“ሪፖርታዥ”

የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ለሀገሪቱ ፖልሲ ቀረፃ ግብዓት ከመሆኑም ባሻገር የዜጎችን ሁለንተናዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ጉልህ ድርሻ አለው የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ በሀገር ደረጃ በአዋጅ 760/2004 ፤ በተሻሻለው 1049/2009  ተደንግገው  ለሰብዓዊ፣ማህበራዊና ፖለቲካዊ መብቶች እንድሁም ኢኮኖሚያዊ ተጠቃምነትን በቋሚነት ማረጋገጥ የሚያስችል ህጋዊ መረጃ ለዜጎችና ለመንግስት ለማቅረብ የሚሰራ ዘርፍ ነው፡፡  የሲቪል መረጃ ምዝገባ ከየትኛውም መረጃ በላይ አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበት ከፌደራል ጀምሮ…

Read More

ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በኢትዮጵያ የደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ ኤምባሲ የልዑካን ቡድን ጋር መከሩ ።

የደቡብ ሱዳን ኤምባሲ መልዕክተኞች በሁለቱ ወዳጅ ሀገራት ድንበር አከባቢ የሚፈጠሩ ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት ቀጠናዊ ትስስርን ለማጠናከር ያለመ ምክክር በቦንጋ ከተማ አካሂዷል። በሁለቱ ወዳጅ ሀገራት መካከል የቆየውን ታሪካዊ ወዳጅነት በማስቀጠል የህዝብ ለህዝብ ግኑኝነት እና ማህበራዊ እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ትስስር በማስቀጠል እንዳለበት በውይይቱ ተመላክቷል። ክልሉ ከደቡብ ሱዳን ሪፑብሊክ ጋር ሰፊ ድንበር የሚጋራ በመኾኑ፥ በድንበር አከባቢ የሚከሰቱ ችግሮችን በዘላቂነት…

Read More

2017 ዓ/ም የአንደኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ የስድስተኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተና በይፉ ተጀምሯል

በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ2ኛ ዙር የሚሰጠው የአንደኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ የስድስተኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተና በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ሁሉም አካባቢ በይፉ ተጀምሯል፡፡ ፈተናው ከዚህ በፊት ሲሰጥ ከነበረበት ሂደት በተሻለ ሁኔታ ለመስጠት ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ፣ የፈተና አዘገጃጀትና አሰጣጥ ስታንዳርድ በጠበቀና ወጥ በሆነ መንገድ መዘጋጀቱ ኩረጃን በማስቀረት የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ እንዲቻል እየተሠራ ላለው ተግባር ጉልህ ሚና እንዳለው…

Read More

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ አመራሮች ሹመት አጸደቀ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢን እና የሥራ አመራር አባላትን ሹመት አፅድቋል። 6ኛው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4 አመት የስራ ዘመን 36ኛው መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል። ምክር ቤቱ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ አቶ ተስፋዬ ንዋይ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አድርጎ ሾሟል፡፡ እንዲሁም አቶ ተክሊት ይመስል እና ወ/ሮ ነሲም አሊ የምርጫ ቦርድ…

Read More

ከለውጡ ወዲህ የሴቶችን ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት ለማሳደግ በተሰሩ ስራዎች መሠረታዊ ለውጥ እየተመዘገበ መሆኑን የኢፌዲሪ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ

የኢፌዴሪ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ጋር በመተባበር ጾታን መሰረት ያደረገ ጥቃት፣ ጎጅ ልማዳዊ ድርጊቶችና የህፃናት ጉልበት ብዝበዛ ለመከላከልና ለማስቆም የተዘጋጀ የንቅናቄ መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው። የኢፌዲሪ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሒክማ ኬይረዲን በመድረኩ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልእክት ከለውጡ ወዲህ የሴቶችን ተሳትፎ እና…

Read More

ተረጂነትና ልመናን ለማስቀረት ሁሉ አቀፍ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኝ የዞን ዋና አስተዳዳሪዎች ተናገሩ ፡፡

አስተዳዳሪዎቹ ተረጂነትና ልመናን ለማስቀረት ችግሮችን በራስ አቅም የመሸፈን አቅም እየተፈጠረ ይገኛልም ብለዋል ፡፡ ተረጂነትና ልመና እንደ ሀገር መለመድ የለበትም ያሉት የቤንች ሸኮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍቲን አመራሩ ከህብረተሰቡ ጋር በመወያየት በራስ አቅም ችግሮችን ለመቅረፍ ምርትና ምርታመነትን ለማሳደግ መግባባት ላይ መደረሱን ተናግረዋል ፡፡ በዚህም በሰው ሰራሽና በተፈጥሮ አደጋ የሚከሰተውን ችግር ለመቅረፍ እንዲያስችል በዞኑ ከተለየው…

Read More

ከቡናው ዘርፍ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ቡና፣ሻይና ቅመም ባለስልጣን ከክልሉ የምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም የበጀት ድጋፍ በቡና ዕሴት ሰንሰለት ዙሪያ በተደረገ ጥናት ውጤት ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ በቦንጋ እየተካሄደ ይገኛል ። መድረኩን በመክፈቻ ንግግር የከፈቱት የክልሉ ቡና ፣ ሻይና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ አስራት መኩሪያ የመድረኩ ዓላማ በተለዋዋጭ ዓለም ውስጥ በቡናው…

Read More

ክልላዊ ፀጋዎችን በአግባቡ በመቀጠም የ2ኛ የአርበኝነት ምዕራፍ ተጋድሎ በአግባቡ መወጣት እንደሚገባ ተገለጸ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን፤በአደጋ ስጋት ስራ አመራር ስርዓት ግንባታና ሰብዓዊ ድጋፍ በራስ አቅም ግንባታ ትግበራ ማዕቀፎች ዙሪያ የባለድርሻ አካላት የምክር መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የክልሉ የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን፥ተፈጥሮአዊና ሰው-ሰራሽ አደጋዎችን ተከትሎ የዓለም-አቀፍ ለጋሽ አገሮች የሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦት በየጊዜው በከፍተኛ ደረጃ እያሽቆለቆለ እንደሚገኝ…

Read More