Trendings

በ2017/18 የመኸር ግብርና ስራዎች ከሚለማው ከ401 ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ 17.5 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማግኘት እንደሚሰራ የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ

በመኸር የግብርና ስራዎች ከ126 ሺህ በላይ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያም ጥቅም ላይ እንደሚውል ታውቋል። አልቆ ማቀድ፣አልቆ መስራት ለምርታማነት ዕድገት! በሚል መሪ ቃል የግብርና መኸር ስራዎች ንቅናቄ መድረክ በቦንጋ ከተማ ተጀምሯል። በንቅናቄው መድረክ የተገኙት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው በክልሉ በግብርናው ዘርፍ ያለውን እምቅ አቅም ለመጠቀም በርካታ ስራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል። ባለፉት ዓመታትም…

Read More

በቅርቡ የኢትዮጵያን ቱባ ባህል የሚያስተዋውቅ የባህል ቡድን ወደ ተለያዩ የዓለም ሀገራት ይጓዛል

የኢትዮጵያን መልካም ገጽታ የሚገነቡ የኪነጥበብ ስራዎች በተለያዩ የዓለም ሀገራት የማቅረብ ተግባር ተጠናክሮ ቀጥሏል አሉ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ነብዩ ባዬ። ሚኒስትር ዴኤታው እንዳሉት፤ የኢትዮጵያን መልካም ገጽታ ከፍ የሚያደርጉ በርካታ ተግባራት በባህልና ኪነጥበብ ዘርፎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። በዚህም የኢትዮጵያን ብዝሃ ባሕልና የጥበብ ስራዎችን በማስተዋወቅ ገጽታን የመገንባት ተግባራት በስፋት መከናወናቸውን ጠቅሰዋል። ይህንንም ተከትሎ በተለይ በሰርከስ እና በስዕል ዘርፍ…

Read More

በክልሉ ስፖርት ከመዝናኛነት ባለፈ ማህበራዊ ፣ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ጠቀሜታው እየጎላ መምጣቱ ተጠቆመ ።

የአላየሁ መላኩ አትሌቲክስ ክለብ ሁለተኛ ዓመት የምስረታ በዓልን በማስመልከት የ5 ኪሎሜትር ህዝባዊ የጎዳና ላይ ሩጫ በገዋታ ወረዳተካሂዷል ። “አኩሪ አትሌቶችን በማፍራት የሀገራችንን ለውጥ እናረጋግጣለን ” በሚል መሪ ቃል በካፋ ዞን ገዋታ ወረዳ በሂንጊዶ ከተማ በተደረገው የጎዳና ላይ 5 ኪሎሜትር ሩጫ ከ300 በላይ ወንዶችና ሴቶች ተሳትፈዋል ። በመርሃግብሩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የወረዳው ምክትል ዋና አስተዳዳሪ አቶ…

Read More

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልልን ምን ያህል ያውቃሉ?

ባለፉት ተከታታይ ሳምንታት ‘’የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልልን ምን ያህል ያውቃሉ?’’ በሚል አምድ ሥር አጠቃላይ የክልላችንን ገጽታ፣  የምዕራብ ኦሞ፣ የካፋ፣ የዳዉሮና የቤንች ሸኮ ዞኖችን አጠቃላይ ገጽታ የሚያሳዩ ጽሁፎችን እንደየቅደምተከተላቸው ለውድ አንባቢዎቻችን አድርሰናል፡፡ በዚህ ሳምንት ደግሞ ከክልላችን ዞኖች አንዱ የሆነውን የሸካ ዞንን እንቃኛለን፡፡ መልካም ንባብ! የሸካ ዞን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ውስጥ ከሚገኙ ስድስት …

Read More

ከክልሉ ሁሉም አከባቢዎች የተወጣጡ የኮሙኒኬሽንና ሚዲያ አመራሮች እና ባለሙያች እንዲሁም የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ተመለከቱ

ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጽያ ህዝቦች ክልል ከሁሉም አከባቢዎች የተወጣጡ የኮሙኒኬሽንና ሚዲያ አመራሮች እና ባለሙያዎች እንዲሁም የኪነጥበብ ባለሙያዎች በቦንጋ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ተመልክተዋል። የኮሙኒኬሽንና ሚዲያ አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም የኪነጥበብ ባለሙያዎች በቦንጋ ከተማ በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ከመደመር ትውልድ መጽሐፍ ሽያጭ ከሚገኘው ገቢ ከ40 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እየተገነባ የሚገኘውን የመደመር ትውልድ የቤተ መጽሐፍት…

Read More

የኪ-ጥበብ ባለሙያዎች አሰባሳቢ ትርክት በመፈጠርና በማስረጽ ረገድ የጎላ አበርክቶ አላቸው፦ አቶ ማስረሻ በላቸው

“ሀገር እና ጥበብ፤ ጥበብ ለኢትዮጵያ ማንሰራራት!” በሚል መርህ ቃል ለደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች የተዘጋጀ ክልላዊ የውይይት መድረክ በቦንጋ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል። በመድረኩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው፥ የኪ-ጥበብ ባለሙያዎች አሰባሳቢ ትርክት በመፈጠርና በማስረጽ ረገድ የጎላ አበርክተው እንዳላቸው ተናግረዋል። ኪነ-ጥበብ በሀገር ግንባታ፣ ታሪክና ትርክት…

Read More

የሚኒስትሮች ምክር ቤት የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳለፈ

የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 47ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል። ምክር ቤቱ ያሳለፋቸው ውሳኔዎች ቀጥሎ ቀርቧል፡- 1. በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው የ2018 በጀት ዓመት የፌዴራል መንግስት ረቂቅ የበጀት አዋጅ ላይ ነው፡፡ የ2018 ዓ.ም የፌዴራል መንግስት በጀት በአስር ዓመቱ መሪ የልማት ዕቅድ ላይ የተቀመጡ ግቦችን ከማስፈጸም፤ የሀገር ደህንነትን ከማስጠበቅ፣ ምርትና ምርታማነትን ከማሳደግ፣…

Read More

ባለፉት የለውጥ አመታት በክልሉ እየተገነቡ ያሉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች በመፍታት ሚናቸው የጎላ መሆኑ የኮሙዩኒኬሽንና የሚዲያ እና የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች ገለፁ

”ዓላማ ተኮር ተግባቦት፣ለሀገር ግንባታ” በሚል መሪ ቃል በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ከሁሉም አከባቢ ከተወጣጡ የኮሙዩኒኬሽንና የሚዲያ ባለሙያዎች እና የኪነ-ጥበብ ሙያተኞች ጋር የውይይት መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው። የኮሙዩኒኬሽንና የሚዲያ እና የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች ከውይይት መድረኩ ጎን ለጎን በክልሉ ቦቦንጋ ከተማ ከመደመር ትውልድ መጽሐፍ ሽያጭ ገቢ እየተገነባ ያለውን የመደመር ትውልድ ቤተ መጻሕፍት እና በርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት…

Read More

በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልፅግና ፓርቲ ም/ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ 2ኛውን የአካባቢ ብክለት መከላከል ሀገራዊ ንቅናቄ በይፋ አስጀምረዋል።

አቶ አደም ፋራህ በማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት÷ የአካባቢ ጥበቃ የቅንጦት ጉዳይ ሳይሆን የብልጽግናችን መሰረት ነው ብለዋል። የአካባቢ ጥበቃ ስራዎች የዜጎች ጤና እንዲጠበቅና ማህበራዊ ኑሯቸው እንዲሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ገልጸው÷ መንግስት ጽዱ ኢትዮጵያን ለመፍጠር በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር፣ በኮሪደር ልማት፣ በታዳሽ ኃይል አጠቃቀም ላይ በርካታ ስራዎች መስራቱን ተናግረዋል። በንቅናቄው የግንዛቤ ማስጨበጫ፣ የማህበረሰብን ተሳትፎ ማጎልበት፣…

Read More

ሪፖርታዥ

የአውሮፓ ህብረት ደንብ ከደን ጭፍጨፋ ነፃ የሆኑ ምርቶች (EUDR) በአውሮፓ ኅብረት ገበያ ላይ የሚቀርቡ ምርቶች ለደን መጨፍጨፍ አስተዋጽኦ እንዳያደርጉ ለማረጋገጥ ያለመ ደንብ ነው። ደንቡ ሰባት ቁልፍ ምርቶች እና ተዋጽኦዎች ከደን መጨፍጨፍ የፀዱ መሆናቸውን ለማረጋገጥ የንግድ ድርጅቶች ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የሚጠይቅ መሆኑም ተመላክቷል።ደንቡ የአውሮፓ ህብረት አረንጓዴ ስምምነት አካል ሲሆን የአውሮፓ ህብረት ለአለም አቀፍ የደን ጭፍጨፋ እና…

Read More