በክልሉ በ2017 በጀት ዓመት የተለያዩ ደረጃ እና ዓይነት ያላቸው 44 የከተማ ፕላኖች መዘጋጀታቸውን በክልሉ ከተሞች ፕላን ኢንስቲትዩት አስታወቀ
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግሥት ከተሞች ፕላን ኢንስቲትዩት የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማ እና በፕላን ዝግጅትና ትግበራ ዙሪያ ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በቴፒ ከተማ እያካሄደ ይገኛል። በመድረኩ የተገኙት የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር የማታለም ቸኮል እንደገለጹት፤መንግስት የሀገራችን ከተሞች የአፍርካ የብልጽግና ተምሳሌት እንዲሆኑ በኮሪደር ልማት ከተሞችን ለማስዋብ እና ለማዘመን ሰፊ ተግባራትን እያከናወነ…
