ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የፕሪቶሪያው ስምምነት ከፍተኛ ጥቅም ማስገኘቱን ገለጹ
የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ከፍተኛ ጥቅም ማስገኘቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ÷ ለሰላም ባለን ከፍተኛ ጉጉት ያሸነፍነውን ጦርነት አቁመን ለሰላም ድርድር ተቀምጠናል ሲሉ አስታውሰዋል፡፡ በኢትዮጵያ ታሪክ እያሸነፈ ለድርድር የተቀመጠ መንግስት እንደሌለም ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተናገሩት፡፡ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ለብዙዎች ልምድ የሚሰጥ ታሪካዊ ስምምነት መሆኑን አውስተው÷…
