የኢንተርፕሪነርሽፕ ልማት ዕቅድን ለማሳለጥ ከ10ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ግንዛቤ መፍጠር መቻሉ ተገለፀ።

የኢንተርፕሪነርሽፕ እና ኢኖቬሽን ሀሳብ ላይ ያተኮረ ስልጠና ለቦንጋ ዩንቨርስቲ መምህራን እና አካዳሚክ የስራ ሃላፊዎች እየተሰጠ ነው ፡፡ በኢንተርፕሪነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ኘሮጄክቶች አስተባባሪ እና አሰልጣኝ አቶ ኢዮብ እምሩ እንደተናገሩት፣የኢንትርፕሪነርሽፕ እና ኢኖቬሽን ሃሳብ ይበልጥ እንዲሰርጸና ትርጉም ያለው ለውጥ እንዲያመጣ የግንዛቤ ስራ ላይ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ከ10ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጐች በስራ ዕድል…

Read More

ማዕከሉ በተመረቀ በአጭር ጊዜ ውስጥ በክልሉ ለሚገኙ በርካታ ደንበኞች የአንድ ማዕከል አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ ተገለጸ

‎የደቡብ ምዕራብ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት በተመረቀ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለ318 ደንበኞች የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጠቱን የክልሉ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ማዕከል ምክትል ስራ አስፈፃሚ አቶ አህመድን አወል ገልጸዋል ‎በማዕከሉ በገቡ በ5 የክልልና በ4 የፌዴራል ተቋማት ስር የሚገኙ 28 አገልግሎቶችን በተቀላጠፈ መልኩ በአንድ ማዕከል ለዜጎች እየተሰጠ መሆኑም ተጠቁሟል። ‎ማዕከሉ በተመረቀ በአጭር ጊዜ ውስጥ 318 አካላት…

Read More

ጥምር ግብርናን በማስፋፋት የአምራቾችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ማሳደግ እንደሚገባ ተገለጸ።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የደን፣ አከባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ቢሮ በFOLUR ፕሮጀክት፣ በተመረጡ ሁለት ወረዳዎች ጥምር ግብርናን ለማስፋፋት ያለመ የባለድርሻ አካላት ውይይት በቦንጋ ከተማ ተካሂዷል። ቀጣይነት ያለውን ጥምር የግብርና ስራዎችን በማስፋፋት የአምራቾችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ማሳደግ እንደሚገባም ነው የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ለማ ገ/ሚካኤል የገለጹት። በፕሮጀክቱ በተመረጡ ሁለት ወረዳዎች የጥምር ግብርናን ውጤታማ በሆነ መልኩ…

Read More

የታሪክ ተመራማሪው ላጲሶ ጌ’ዴሌቦ (ፕ/ር) …

ላጲሶ ጌ’ዴሌቦ (ፕ/ር) የተወለዱት ከአባታቸው አቶ ዴሌቦ ሸለሞ እና ከእናታቸው አሹሬ ደከጉ ግንቦት 1930 ዓ.ም በሀዲያ ዞን በቀድሞው አጠራር በሶሮ አውራጃ በኩፋና ቀበሌ ያሮ በተባለው መንደር ነው፡፡ ላጲሶ ጌ’ዴሌቦ (ፕ/ር) ገና የ13 ዓመት ልጅ ሳሉ ነበር በአንድ ሳምንት ውስጥ እናትና አባታቸውን ያጡት፡፡ በወቅቱም ብዙ ችግር አጋጥሟቸው እንደነበርና ከሦስት ዓመት በኋላ በአንድ ዘመዳቸው እርዳታ ሆሳዕና ከተማ…

Read More

ለበጋ መስኖ ስንዴ የምርጥ ዘርና የማዳበሪያ አቅርቦት በስፋት እየተከናወነ ነው – ግብርና ሚኒስቴር

ለ2018 በጀት ዓመት የበጋ መስኖ ስንዴ ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድጉ የምርጥ ዘርና የማዳበሪያ አቅርቦት በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ግብርና ሚኒስቴር አስታውቋል። ሚኒስቴሩ ከ767 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በማረስ ከዚህ ውስጥም ከ359 ሺህ ሄከታር መሬት በላይ በዘር መሸፈኑን ገልጿል። የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ የአርሶ አደሩን የስራ ባህል በመቀየር በዓመት ከሁለት ጊዜ በላይ እየተመረተ ይገኛል።…

Read More

በኢትዮጵያ የሚካሄደው አህጉራዊ የመሬት ፖሊሲ ጉባኤ

ስድስተኛው የአፍሪካ የመሬት ፖሊሲ ኮንፍረንስ ከዛሬ ጀምሮ በአዲስ አበባ ይካሄዳል። “የመሬት አስተዳደር፣ ፍትህ እና ካሳ ለአፍሪካውያንና ለዘርዓ አፍሪካውያን” በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የሚካሄደው ኮንፍረንስ መሪ ሀሳብ ነው። የአፍሪካ ህብረት፣ የአፍሪካ ልማት ባንክ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) ኮንፍረንሱን በጋራ አዘጋጅተውታል። ከአፍሪካ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ታሪካዊ እና የአካባቢ ጉዳዮች ጋር የተጣጣሙና ለነባራዊ እውነታዎች…

Read More

ማጂ የኢንግሊዝ ቆንስላ ጽ/ቤት የነበራት ከተማ!

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ከሚገኙ ዞኖች አንዱ የኾነው የምዕራብ ኦሞ ዞን በወርቅ ክምችት እና በሌሎች የከበሩ ማዕድናት እንዲሁም በተፈጥሮ ሀብት የሚታወቅ አከባቢ ነው። በዞኑ ከሚገኙ መዋቅሮች መካከል አንዱ ደግሞ የማጂ ቱም ከተማ አስተዳደር ሲሆን፣ የክልሉ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ከሰሞኑ በጥንታዊቷ የማጅ ከተማ ተዘዋውሮ ምልከታ አድርጓል። የማጂ ከተማ፥ የቀድሞው ካፋ ክፍለሀገር አውራጃ መቀመጫ በመኾን…

Read More

የመገጭ ግድብ የወንዝ ቅልበሳ ሥራ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቅቋል – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር)

የመገጭ መስኖ ልማት ፕሮጀክት የወንዝ ቅልበሳ ሥራ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቅቋል አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ ÷ በጎንደር በነበረን ጉብኝት የመገጭ የመስኖ ልማት ፕሮጀክትን የሥራ ሁኔታ ገምግመናል ብለዋል። ፕሮጀክቱ 870 ሔክታር መሬት ላይ ያረፈ ሲሆን ÷ ሥራው ሲጠናቀቅ 17 ሺህ ሔክታር በመስኖ አቅርቦት ይሸፍናል ተብሎ እንደሚጠበቅ አስረድተዋል፡፡ የፕሮጀክቱ…

Read More

አባላቱ በተሰማራበት የስራ መስክ ውጤታማ ተግባራትን በመፈጸም የፓርቲውን ድርብ ተልዕኮዎችን ከወትሮው በተለየ መልኩ ለማሳካት መትጋት አለበት፦ አቶ ሳምሶን መለሰ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የአስተዳደር ዘርፍ የብልጽግና ህብረት የ2018 የ1ኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም የአባለት ኮንፈረንስ ተካሂዷል። የህብረቱ ሰብሳቢ አቶ ሳምሶን መለሰ እንደገለጹት የህብረቱ ዓባላት ፓርቲው ያነገባቸውን ተልዕኮዎቹን ከግብ ለማድረስ እያደረገ ያለው የተቀናጀ ጥረት አበረታች ለውጦችን ማስመዝገብ ችሏል። 2018 ዓም የህብረቱ አባላቱም የኢትዮጵያን የማንሰራራት ዘመን ለማጽናት በፓርቲው የአሰራር ስርዓት መሠረት ብርቱ ውይይት በማካሄድ ተጭበጭ…

Read More

ተገቢ የኤች.አይ. ቪ /ኤድስ ምርመራና የህክምና አገልግሎት በመስጠት የበሽታውን ስርጭት መቀነስ እንደሚገባ ተገለጸ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ዳይሬክቶሬት የ2017 በጀት ዓመት ዓመታዊ አፈጻጸምና እና የ2018:ዓ/ም 1ኛ ሩብ ዓመት የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ከእናት ወደ ልጅ እንዳይተላለፍ መከላከል (PMTCT)፣ የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር(EXCA) እና የጉበት ቫይረስ (Hepatitis) ምርመራና ህክምና የአፈጻጸም ግምገማ መድረክ በታርጫ በማካሄድ ላይ ይገኛል። በመድረኩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊና…

Read More