በክልሉ የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል በተሰጠው ትኩረት መሻሻሎች እየታዩ ነው:- ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል፣ ትምህርት ቢሮ 2ተኛውን የትምህርት አስተዳደር ጉባኤ በታርጫ ከተማ እያካሄደ ይገኛል። በጉባኤው ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)፥ በክልሉ የተማሪዎች ውጤት ለማሻሻል በተሰጠው ትኩረት መሻሻሎች እየታዩ መኾኑን ተናግረዋል። በማኅበረሰብ ተሳትፎ የትምህርት ቤት ደረጃ ማሻሻልና የትምህርት ግብዓት ከማሟላት አኳያ አበረታች ውጤት መመዝገቡን የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሩ፥ በተያዘው በጀት ዓመትም…
