በክልሉ በየደረጃው የመልካም አስተዳደር ጉዳዮችን መፍታት የሚያስችል ተቋማዊ ፎረም ተቋቁመው ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት ክልል ዓቀፍ የመልካም አስተዳደር እና ቅሬታ አቤቱታ ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በቦንጋ ከተማ እያካሄደ ነዉ በመድረኩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድርና መስተዳድር ምክር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተረፈ ዘዉዴ፤ ከማህበረሰቡ በየደረጃው የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፈታት ህዝቡን ለልማት ከማነሳሳት ባለፈ ህዝቡን ከመንግሥት ጋር በማቀራረብ መልካም ሥራዎች እንዲከናወኑ ዕድል እንደሚፈጥር…
