ቡናን ቴክኖሎጂን ተጠቅሞ የምርት ጥራትን በማስጠበቅ ለዓለም ገበያ በማቅረብ የውጭ ምንዛሬን ለማሳደግ እየተሰራ ነዉ፦ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት በበሸካ ዞን የዘመናዊ ቡና ልማት ኢንቬቲቭ ማስጀመሪያና ለባለድርሻ አካላት ግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በቴፒ ከተማ እየተካሄደ ነዉ። የንቅናቄ ዓላማ በዞኑ ያለውን ሰፊ የቡና ልማት አቅም በመጠቀም፣ አርሶ አደሩ ከባህላዊ አሰራር ወጥቶ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ የቡና ልማት እንዲያከናውን ለማስቻል መሆኑ ተገልጿል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በመድረኩ መክፈቻ ላይ…
