ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር

ዜጎች በዋትሳፕ፣ በቴሌግራም እና በሌሎች የመልዕክት መላላኪያ አማራጮች ለሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች እና የማጭበርበር ድርጊቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር አሳሰበ። ማህበረሰቡ የሳይበር ደህንነት የማስጠበቅ ኃላፊነቱን እንዲወጣም ጥሪ አቅርቧል። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ)፤በኢትዮጵያ የዲጂታል ትስስር መስፋፋትን ተከትሎ በዋትሳፕ (WhatsApp)፣ በቴሌግራም (Telegram) እና በሌሎች የመልዕክት መላላኪያ ፕላትፎርሞች አማካኝነት በዜጎች ላይ የሚሰነዘሩ የሳይበር…

Read More

የጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ መልዕክት

በጽሕፈት ቤታችን ከተገኙት የአሜሪካ ረዳት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክሪስቶፈር ቲ ላንዳው እና የዩኤስ አፍሪካ እዝ አዛዥ ጄነራል ዳግቪን አንደርሰን ጋር ተወያይተናል:: ቀጣይነት ያለው ትብብር እና መከባበርን አፅንዖት ለሰጠው ደማቅ እና ገንቢ ውይይታችን ምስጋናዬን አቀርባለሁ::

Read More

የሺህዎች ድምፅ፣ የአንድ ሀገር ተስፋ፡ የኢትዮጵያ የምክክር ጉዞ

ኢትዮጵያ ልክ እንደ አንዲት ትልቅ እና ጥንታዊት እናት ናት። ማህፀኗ ብዙ ልጆችን አሳድጓል፤ እጆቿ ለብዙዎች መጠለያ ሆነዋል። ነገር ግን ባለፉት ዘመናት ይህች እናት በልጆቿ መካከል በሚፈጠር “አለመደማመጥ” ምክንያት ስትቆስል ቆይታለች። ትላንት፡ የዝምታና የጩኸት ዘመን ለረጅም ጊዜ በኢትዮጵያ ሰማይ ስር መነጋገር ብርቅ ነበር። አንዱ ሲናገር ሌላው የማይሰማበት፣ የሃሳብ ልዩነት እንደ ክህደት የሚቆጠርበት፣ እና ቅሬታዎች በጠረጴዛ ዙሪያ…

Read More

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌድዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ከአሜሪካው ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ

የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌድዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ዛሬ በጽሕፈት ቤታቸው የአሜሪካውን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክሪስቶፈር ላንዳውን ተቀብለው አነጋግረዋል። በውይይታቸውም በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ መካከል ያለውን የቆየ ግንኙነት ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ መክረዋል፡፡ በተጨማሪም በቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ዙሪያ ሰፊ የሐሳብ ልውውጥ አድርገዋል። ኢትዮጵያና አሜሪካ ለ120 ዓመታት የዘለቀ ታሪካዊና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላቸው ሲሆን፤ የዛሬው ውይይትም…

Read More

የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ የአረጋውያን መንደር በመገንባት የትናንት ባለታሪኮችን የመንከባከብ ስራ አጠናክሮ መቀጠሉ ተጠቆመ

‎ዩኒቨርሲቲው ከምርምርና ትምህርት ስራ ጎን ለጎን በተለያዩ ማሕበረሰብ አቀፍ አገልግሎቶች በማከናወን ውጤታማ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑም ተጠቁሟል። ‎በተለይም ጧሪ ደጋፊ የሌላቸውን አረጋውያን ለመደገፍ የአረጋውያን መንደርን በማመቻቸት ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ደገላ ኤርገኖ (ዶ/ር) ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ተናግረዋል፡፡ ‎የትናንት ባለታሪክ እና የሀገር ባለውለታ የሆኑ አረጋውያንን ከወደቁበት በማንሳት ዩኒቨርሲቲው ባስገነባው መንደር እየተንከባከበ መሆኑን ገልጸዋል። ‎ተቋሙ በተለያዩ…

Read More

የካፋ ዞን ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ ማካሄድ ጀምሯል::

ምክር ቤቱ በመደበኛ ጉባኤው ያለፈውን 4ኛ ዙር 12ኛ ዓመት 25ኛውን ጉባኤ ቃለጉባኤ መርምሮ በሙሉ ድምጽ በማጽደቅ ነው የጀመረው:: በመቀጠል ምክር ቤቱ የዞኑን ዋና አፈ ጉባኤ ሹመት ያፀደቀ ሲሆን በዚህም ክብርት ወ/ሮ አሚናት ሀሰን የካፋ ዞን ዋና አፈጉባኤ እንዲሆኑ በዞኑ ዋና አስተዳዳሪ የቀረበውን የሹመት ፕሮፖዛል ተቀብሎ በሙሉ ድምጽ በማጽደቅ ጉባኤ ተጀምሯል:: የዞኑ ምክር ቤት ጉባኤ በሚኖረው…

Read More

የተፋሰስ ልማት ሥራ ከተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ በተጓዳኝ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የጎላ ፋይዳ አለው – አቶ ማስረሻ በላቸው

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል፣ የ2018 ዓ/ም የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ የተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በምዕራብ ኦሞ ዞን፣ መኒት ጎልዲያ ወረዳ እየተካሄደ ይገኛል። በመርሐግብሩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው፥ በክልሉ ከዚህ ቀደም በተከናወነው የተቀናጀ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ አመርቂ ውጤት ተመዝግቧል ብለዋል። የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ሥራ ከተፈጥሮ ሀብት…

Read More

ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል፣ የ2018 ዓ/ም የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ የተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው በተገኙበት በምዕራብ ኦሞ ዞን፣ መኤኒት ጎልዲያ ወረዳ እየተካሄደ ይገኛል። በክልሉ እየተከሰተ ያለዉን የመሬትና የተፈጥሮ ሀብት መመናመን እና የአፈር መሸርሸርን ለመከላከል የመሬት ፣ የውሃና የሰው ሀብት መጠበቅ ፣ ማልማትና በላቀ ደረጃ በማቀናጀት ጥቅም…

Read More

“በሀገሩ ሉዓላዊነት የማይደራደር ሠራዊት ማፍራት ተጠናክሮ ይቀጥላል”- ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ

ወቅቱን የሚመጥን ሠራዊት የማፍራት ተልዕኮ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ተናገሩ። ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ አየር ኃይል ላስመረቃቸው እጩ መኮንኖች ማዕረግ የማልበስ ሥነ-ሥርዓት አከናውነዋል። በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግርም፣ “ኢትዮጵያ ቀደምት ሀገር በመሆኗ እና ካላት የጂኦ-ፓለቲካ አቀማመጥ አንጻር ጠላት ተደጋጋሚ ትንኮሳ ቢያደርግባትም ጀግኖች አርበኞች የተከበረች ሀገርን አስረክበውናል” ብለዋል። በዘመናዊ…

Read More

ሀገራዊ አጀንዳ ምን ዓይነት ቅርፅ ሊኖረው ይችላል?

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአዋጅ ቁጥር 1265/2014 መቋቋሙ የሚታወስ ነው፡፡ በዚሁ አዋጅ መግቢያ ላይ በሀገራችን ኢትዮጵያ በሚገኙ የተለያዩ የፓለቲካ እና የሀሳብ መሪዎች እንዲሁም የህብረተሰብ ክፍሎች መካከል እጅግ መሰረታዊ በሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የሀሳብ ልዩነቶች እና አለመግባባቶች መኖራቸው ተጠቅሶ ይህም ለኮሚሽኑ መመስረት እንደምክንያት ተቀምጧል፡፡ ‘’እጅግ መሰረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች’’ ሊባሉ የሚችሉ ጉዳዮች የትኞቹ ናቸው? ይህንን ጉዳይ ለመረዳት…

Read More