ኢትዮጵያ የተዘጋባት በር በመከፈቱ ለዘርፉ ትልቅ ዕድል ነዉ – አለሙ ስሜ (ዶ/ር)
ኢትዮጵያ የተዘጋባት በር በመከፈቱ ለዘርፉ ትልቅ ዕድል መሆኑን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር የ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያ አጋማሽ የሴክተር አፈጻጸም በወላይታ ሶዶ ከተማ እየገመገመ ነው፡፡ ዓለሙ ስሜ(ዶ/ር) በወቅቱ፥ ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ የሁሉም ዘርፎች ደም ስር በመሆኑ በጋራ ልንሠራ ይገባል ነው ያሉት። በዚህም ባለፉት ጊዜያት በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዘርፍ የተሳኩ ተግባራት መፈጸማቸውን…
