ሕብረተሰቡ ከሐሰት ፕሮፓጋንዳ በመራቅ የሕግ የበላይነት የተረጋገጠበት ክልል ለመገንባት እንዲረባረብ ጥሪ ቀረበ::
በአማራ ክልል የተገኘው አንጻራዊ ሰላም የተሟላ እንዲሆን ሁሉም የሕብረተሰብ ክፍል ከሐሰት ፕሮፓጋንዳ ራሱን በማራቅ የሕግ የበላይነት የተረጋገጠበት ክልል ለመገንባት በጋራ እንዲረባረብ ጥሪ ቀረበ፡፡ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ዛሬ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ መግለጫ አውጥቷል፡፡ በመግለጫውም በቀጣይ ልማቱን አጠናክሮ ለማስቀጠልና ሰላምን ለማረጋገጥ ውስጣዊ አንድነትንና የውስጥ ሰላምን የበለጠ ማጽናት ይገባል ብሏል፡፡ የክልሉ መንግሥት መግለጫ ሙሉ ቃል ቀጥሎ ቀርቧል፡-…
