በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የጥምቀት በዓል እየተከበረ ነው

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የጥምቀት በዓል በአዲስ አበባ ልደታ ማሪያም ካቶሊክ ካቴድራል ቤተክርስቲያን እየተከበረ ይገኛል። በበዓሉም የሃይማኖት አባቶች፣ የእምነቱ ተከታዮች ምዕምናንና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል። በዓሉ በቅዳሴ፣ በፀሎት፣ በዝማሬ፣ በምስጋና እና በሌሎች ሃይማኖታዊ ሥነ-ሥርዓቶች በድምቀት እየተከበረ መሆኑን ኢዜአ ዘግቧል። በዓሉ በመላው ሀገሪቱ ባሉ የካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ተከብሮ እንደሚውልም ተገልጿል ሲል ደሬቴድ ዘግቧል።

Read More

ምክርቤቱ የመንግስትና የህዝብ ንብረትን ለማስመለስ የነበረውን የሕግ ክፍተት የሚሞላ አዋጅ አጸደቀ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስትና የህዝብ ንብረትን ለማስመለስ የነበረውን የሕግ ክፍተት የሚሞላ የንብረት ማስመለስ አዋጅን አጽቋል። ምክር ቤቱ ዛሬ ባካሄደው14ኛ መደበኛ ስብሰባው የንብረት ማስመለስ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ የሕግና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሃሳብ መርምሮ በአብላጫ ድምጽ አጽድቋል። አዋጁ በሕገ-ወጥ መንገድ የተፈራን ንብረት ማስመለስ የሚያስችሉና የሕግ-ተጠያቂነትን የሚያስከትሉ ድንጋጌዎችን የያዘ ነው። የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ…

Read More

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ከ700 በላይ ቀበሌዎች የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ በዲጂታል ምዝገባ ሥራ / Online / ውስጥ እንዲገቡ ተደርጓል፡፡

የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ተግባራትን ለማሳካት እንዲቻል ከ2 ሚሊዮን 443 ሺህ 600 ብር በላይ የሚገመት የኤሌክትሮኒክስ ግዥ መፈጸሙም ተገልጿል ፡፡ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ሠላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊና የወሳኝ ኩነቶች ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሰለሞን ደነቀ እንደገለጹት የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባን በክልሉ በሚገኙ ሁሉም መዋቅሮች ወደ ድጅታል ምዝገባ ሥራ /Online / ውስጥ እንዲገቡ…

Read More

ምሁራን የህዝቡ አጀንዳ አጀንዳችን ከሆነ ከመነጣጠል ፣ ከመገፋፋትና ከመበተን ይልቅ ለአንድ አላማና ለማህበረሰቡ ለውጥ በጋራ ልንሰራ ይገባል ፦ አቶ ሀብታሙ ካፍትን

3ኛው የቤንች ብሔር ምሁራን ማህበር ጠቅላላ ጉባኤ በሚዛን አማን ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። የቤንች ሸኮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን መድረኩን በንግግር ሲከፍቱ እንደተናገሩት አለም ለዛሬ ስልጣኔ ፣ ዘመናዊነትና ዕድገት የበቃችው በምሁራን የፈጠራ ፣ የጥበብና የምርምር ስራዎች ታግዛ ነው ብለዋል። ዛሬ ላይ በአለማችን እጅግ ሰለጠኑ ፣ በሳይንስና ቴክሎጂ ምጡቅ ሆኑ የሚባሉት ሀገራት ከመሬት ተነስተው ሳይሆን…

Read More

ቼክ ሪፐብሊክ በግብርና ቴክኖሎጂ አቅርቦት ዘርፍ ከኢትዮጵያ ጋር ለመሥራት ቁርጠኛ መሆኗን ገለጸች

ቼክ ሪፐብሊክ በግብርና ቴክኖሎጂ አቅርቦት እና በእንስሳት ልማት ዘርፎች ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር ለመሥራት ቁርጠኛ መሆኗን አረጋገጠች፡፡ የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ከቼክ ሪፐብሊክ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማሪያን ጁርካ ጋር በትብብር በሚሠሩ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ባደረጉት ውይይት፤ በስንዴ ልማት፣ በሌማት ትሩፋትና በአረንጓዴ ዐሻራ አበረታች ውጤት መመዝገቡን አብራርተዋል፡፡ ምርታማነትን ለማሳደግ የሚደረገውን ጥረት ለማጎልበት በግብርና ሜካናይዜሽን ዘርፍ ኢትዮጵያ…

Read More

በ19ኛው የብሔረሰቦች ቀን በዓል የክልሉ ቱባ ባህልና መልካም እሴቶች ጎልተው እንዲወጡ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ መቱ አኩ የበዓሉን አከባበር ቅደመ ዝግጅት ስራዎችን አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል። የክልሉ የብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ መቱ አኩ እንደገለፁት 19ኛው በሀገር አቀፍ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ የብሔረሰቦች ህዝቦች ቀን በዓልን አስመልክቶ የብሔረሰቦች ምክር ቤት ሀገራዊ መሪ ቃሉ ላይ በቂ ግንዛቤ በመያዝ…

Read More

ዜጎች የጡረታ መብታቸውን የሚከበርበትን አሰራር በማሻሻል በአጭር ጊዜ መብታቸውን የሚያስከብሩበት ሁኔታ ማመቻቸቱን የግል ድርጅት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር አስታወቀ

በኢፌዴሪ የግል ድርጅት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር የጅማ ድስትሪክት በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ከባለድርሻ አካላት ጋር በቦንጋ ከተማ መክሯል። በምክክሩ መድረክ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ እንዳሻው ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደሩ ሰላማዊ የኢንዱስትሪ ግንኙነቶችን በመፍጠር ከመንግስት የተሰጠውን ተልዕኮ እየፈጸመ ይገኛል ብለዋል። በዚህም በአሰሪና ሰራተኞች መካከል ጤናማ የስራ ግንኙነት…

Read More

የምክክር ኮሚሽኑ በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም እንዲፈጠር አስተዋጽኦ አለው – የአውሮፓ ህብረት

ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም እና መረጋጋት እንዲፈጠር በማድረግ ገንቢ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው የአውሮፓ ህብረት ገለጸ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት አምባሳደር ሶፊ ፍሮም-ኢመስበርገርን ተቀብለው አነጋግረዋል። ሚኒስትሩ የአውሮፓ ሕብረት ኢትዮጵያ በማኀበረ-ኢኮኖሚ መስኮች ለማሻሻል ለምታደርገው ጥረት ቁልፍ አጋር መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ከሕብረቱ ጋር ያላትን ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር እንደምትሰራና በተለይም በልማት ትብብር፣ በንግድ…

Read More

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተውጣጡ ታዋቂ ሰዎች አጀንዳ የማሰባሰብ ውይይት ዛሬም ቀጥሏል።

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ባዘጋጀው የውይይት መድረክ ከክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች የመጡ ታዋቂ ሰዎች ጋር አጀንዳ የማሰባሰብ ውይይት ተጀምሯል። ኮሚሽነር ዘገየ አስፋው ባስተላለፉት መልዕክት ዛሬ የተሰባሰቡ ታዋቂ ሰዎች በአካባቢያቸው ህዝብን በማስተባበር ብዙ መስራት የቻሉ መሆናቸውን ተናግረዋል ። በሚኖረው የአጀንዳ ማሰባሰብ ውይይት ላይ የምታፈልቁት ሀሳብ በግብታዊ ሳይሆን መሠረታዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ መሆን እንዳለበት ኮሚሽነር ዘገዬ አሳስበዋል ።…

Read More