ምክክሩ ጠንካራ ሀገር ለመገንባት ጉልህ ሚና እንደሚኖረው የ ተሳታፊ ሴቶች፣ ወጣቶች እና አካል ጉዳተኞች ተናገሩ፡፡
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ከሚገኙ 41 ወረዳዎች እና 16 ከተማ አስተዳደሮች በሀገራዊ ምክክር ኮሚሸን እየተካሄደ ባለዉ የአጀንዳ አሰባሰብ መድረክ ከየማህበራዊ መሠረቶች እየተሳተፉ ያሉት ሴቶች፣ ወጣቶች እና አካል ጉዳተኞች፣ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክሩ፣ ሀገር ካገበችበት ውስብስብ ችግሮች ለማላቀቅ ጉሊህ ሚና እንዳለው ተናግረዋል ። በዉይቱ በመሳተፋቸው ደስተኛ ስለመሆናቸውና ምክክሩ ለሴቶች እጅግ በጣም ጠቃሚ መሆኑን የገለጹት የሴቶች ተወካይ…
