Trendings

Getenesh Gebeyehu

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 39ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡

39ኛ መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ውሳኔዎች 1. በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው ብሔራዊ የመካከለኛ ዘመን 2017-2020 የገቢ ስትራቴጂ ላይ ነው፡፡ ስትራቴጂው የታክስ ሥርዓቱን ለማዘመን እና ለግል ኢንቨስትመንቱ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር የታለመ ሲሆን አጠቃላይ የታክስ ፖሊሲዎችን እና አስተዳደራዊ ሪፎርሞችን እንዲሁም ማሻሻያዎችን ለመተግበር የሚያስችል ነው፡፡ ሰትራቴጂው ከ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድ ጋር የተጣጣመ እንዲሆን ተደርጎ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም…

Read More

ከ146 ዓመታት ወዲህ በወርሃ የካቲት 2016 ዓ/ም የሸካቾ ባህላዊ የአስተዳደር መዋቅር ወደ ስራ ከገባ ለመጀመሪያ ጊዜ “ማሽቃሬ ባሮ”የዘመን መለወጫ በዓል በተለያዩ ባህላዊ ክዋኔዎች ተከብሯል።

ፕሮግራሙ በሚክረቾ አባላት ባህላዊ የምርቃት ስነስርዓት በማድረግ በይፋ ነው የተከበረው። በዘመን መለወጫ ስነስርዓት ላይበመገኘት ንግግር ያደረጉት የአንድራቻ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ አየለ አንገሎ የሸካቾ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ “ማሽቃሬ ባሮ ” ባህላዊ እሴቱን ጠብቆ በማልማትና በመንከባከብ ለቀጣይ ትውልድ ለማስተላለፍ የአሁኑ ትውልድ ትልቅ አደራ ያለበት ነው ብለዋል። የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ ዞኑ የኤክስፖርት ምርቶች በስፋት…

Read More

የሸካቾ ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ “ማሽቃሬ ባሮ ” በጌጫ ከተማ መከበር ጀምሯል።

የአብሮነትና የወንድማማችነት የብሔረሰቡ ዘመን መለወጫ “ማሽቃሬ “ባሮ የብሔረሰቡ ተወላጆች ፣ከተለያዩ አካባቢዎች የተጠሩ ተጋባዥ እንግዶች በዓሉ በሚከበርበት ስፍራ በመግባት ላይ ይገኛሉ ። በሸካቾ ብሔረሰብ መለወጫ የክልል ከፍተኛ አመራሮች፣ የተለያዩ ብሔረሰቦች የባህል አባቶች፣የሸካ ብሔረሰብ ገፒታቶዎች እንደሚገኙም ለማወቅ ተችሏል። ማሽቃሬ ባሮ ከስፍራው በኢቢሲ፣በማሻ ኤፍ ኤም 103.8 ሬዲዮ በቀጥታ ከጥቂት ቆይታ በኋላ የሚጀመር ይሆናል። በታጠቅ አበበ

Read More

የትምህርት ስብራትን ለመጠገን በክልሉ የተጀመረውን ሁሉ አቀፍ ተግባርን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ትምህርት ቢሮ ገለፀ

በሀገራችን የትምህርት ጥራት ላይ እያጋጠሙ ያሉ ስብራቶችን ለመጠገን በመንግስት በኩል በርካታ የሪፎርም ስራዎች እየተሰሩ መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልልም ይህንን የትምህርት ጥራት ችግሮችን ለመፍታት በክልሉ በትምህርት ቢሮ በኩል የጀመሩት በርካታ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው የገለፁት የክልሉ ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊና የመማር ማስተመር ዘርፍ ኃላፊ ዶክተር ደስታ ገነሜ ለዚህም በክልሉ አጠቃላይ በትምህርት ስርዓቱ…

Read More

ኢትዮ ቴሌኮም ኮፐር ስዊች ኦፍ የተሰኘ አገልግሎት ይፋ አደረገ

ኢትዮ ቴሌኮም የኮፐር መስመሮችን ወደ ፋይበር በመቀየር ዘመናዊ ባለገመድ ብሮድባንድ ኢንተርኔትና በዳታ ላይ የተመሰረተ የድምጽ አገልግሎት ለማቅረብ “ኮፐር ስዊች ኦፍ” የተሰኘ አገልግሎት ይፋ አድርጓል፡፡ የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ ይፋ የሆነውን አገልግሎት በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ÷ ከዚህ ቀደም የነበረው የኮፐር አገልግሎ በቴሌኮም ኢንዱስትሪው ከ150 ዓመታት በላይ ማገልገሉን ገልጸዋል። በኢትዮጵያም ለ130 ዓመታት ለደንበኞች የባለገመድ መደበኛ…

Read More

የካፈቾ ብሔር የአዲስ ዘመን መለወጫ (ማሽቃሮ) እየተከበረ ይገኛል

የ2017 ዓ/ም የካፈቾ ብሔር የአዲስ ዘመን መለወጫ (ማሽቃሮ) በዓል በደማቅ ህዝባዊ ተሳትፎ የነገስታት መናገሻ በሆነው ‹‹ቦንጌ ሻምበቶ›› በደማቅ ባህላዊ ክዋኔዎች ታጅበው እየተከበረ ይገኛል። የፌዴራል ፖሊሲ ማርች ባንድ ለዕለቱ ክብር እንግዶች ደማቅ አቀባበል አድርገዋል። በበዓሉ ለመታደም ከሀገረ ሩስያ የተገኙ የውጭ ሀገራት ዜጎች የሀገራቸውን ባህል የሚያሳይ የባህል አልባሳትን በመልበስ በበዓሉ ታድመዋል። የካፈቾ ባህላዊ ምክር ቤት (ምክሬቾ) አባላት…

Read More

‹‹የማሽቃሮ›› በዓልን በዩኒስኮ ለማስመዝገብ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ተጀምሯል፦ የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ

የ2017 የካፈቾ የአዲስ ዘመን መለወጫ (ማሽቃሮ) በቦንጋ ከተማ አቅራቢያ በሚገኘው የነገስታት መነገሻ ስፍራ ‹‹ቦንጌ ሻምበቶ›› በድምቀት ተከብሯል። የካፈቾዎች የአዲስ ዘመን (ማሽቃሮ) በዓል ከ1897 በፊት በደማቅ ህዝባዊ ተሳትፎ ይከበረ እንደነበረ ያወሱት የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ ይሁን እንጅ በሀገራችን የዲሞክራሲ ስርዓት እስከሰፍን 1990ዎቹ የበዓሉን አከባቢር ማስቀጠል አለመቻሉን ተናግረዋል። የማሽቃሮ በዓል በ1986 በተካሄደው የመጀመሪያው የካፋ…

Read More

የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች በአዳማ ከተማ የሌማት ትሩፋትና የኢንዱስትሪ ልማት ሥራዎችን ጎበኙ

ከመስከረም 04 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች በአዳማ ከተማ “የህልም ጉልበት ለእምርታዊ እድገት” በሚል መሪ ሃሳብ የአቅም ግንባታ ስልጠና በመሰጠት ላይ ይገኛል። የፓርቲው ፕሬዝዳንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያስጀመሩት የስልጠና መድረክም የፓርቲው አመራር ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ሁኔታዎችን ተገንዝቦ የቀጣይ ተልዕኮን በብቃት መወጣት የሚያስችል እንደሆነ ተገልጿል። የስልጠናው ተሳታፊዎችም በዛሬው እለት…

Read More