በትናንትናው ስንፋጅ ነገን እያጣን ስለሆነ አሰባሳቢ የጋራ ትርክት ያስፈልገናል – ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር)

ኢትዮጵያ ውስጥ በትናንትናው ስንፋጅ ነገን እያጣን ስለሆነ ልክ እንደ ዓድዋ አሰባሳቢ የጋራ ትርክት ያስፈልገናል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 14ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ተገኝተው ከምክር ቤቱ አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በማብራሪያቸውም÷ ኢትዮጵያ ውስጥ በትናንትናው ስንፋጅ ነገን እያጣን በመሆኑ የጋራ ትርክት እጅግ…

Read More

ከሸማቂ ሃይሎች ጋር ውይይት አድርጎ በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት መሞከር አዲስ ነገር አይደለም – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ከሸማቂ ሃይሎች ጋር ውይይት አድርጎ በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት መሞከር አዲስ ነገር ሳይሆን በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለያዩ ሀገራት የሚተገበር መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ፡፡ የኢትዮጵያ መንግስትም በዚሁ አግባብ ከሸኔ ጋር ያለውን ችግር በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ጥረት እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት፤…

Read More

በአማራ ክልል በተደረገው ውይይት ከህዝቡ ሶስት ዋና ዋና ጥያቄዎች ተነስተዋል – ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአማራ ክልል ሁሉም ዞኖች በተደረገው ውይይት ከህዝቡ ሶስት ዋና ዋና ጥያቄዎች መስተዋላቸውን አንስተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 14ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ክልሉን በተመለከተ ምላሽ ሲሰጡ የልማት፣ የህገ መንግስት ማሻሻልና የወሰን ጥያቄዎች በተደረገው ውይይት ከህዝቡ የተነሱ ዋና ዋና አጀንዳዎች ናቸው ብለዋል፡፡ መንግስት በአማራ ክልል…

Read More

በኢትዮጵያ ውስጥ የፖለቲካ ፍላጎትን የማሳኪያ ስልት ልምምድ ሰላምን እየፈተነ ነው፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ባለፉት 50 እና 60 ዓመታት ሃሳብ ይዞ በሃሳብ አሸንፎ ስልጣን የመያዝ ልምምዱ ያልታየ በመሆኑ እንደባህልም እየተወሰደ ያለው የፖለቲካ ፍላጎትን በጠብመንጃ የማሳካት ፍላጎት አንዱ አደገኛ ስብራት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት የሰላም ችግር መሰረቱ የፖለቲካ ፍላጎት ማሳኪያ መንገድ ላይ ያለው ልምምድ መሆኑን…

Read More

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 14ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ሠላምና ፀጥታን በተመለከተ ካነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች መካከል

በኢትዮጵያ የፖለቲካ ፍላጎት የማሳኪያ ስልት (ልምምድ) ችግር አለበት፤ በዚህም ከውይይት ይልቅ ጠመንጃ ማንሳትን ያስቀደመ መሆኑ ትክክል አለመሆኑን አንስተዋል፡፡ በጦርነት የሚገኝ ጥቅም የለም፤ ጥቅም ያለው ከሠላም ነው፤ ይህን ሁልጊዜም መገንዘብና መኖር ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ ከሸኔ ጋር የተካሄደው ድርድር ለሕዝብ ይፋ የምናደርገው የተጨበጠ ጉዳይ ስለሌለ ነው ይፋ ያልተደረገው፤ በቀጣይ ተጨባጭ ጉዳይ ሲኖር ለኢትዮጵያ ሕዝብ ይፋ ይደረጋል፡፡ ከሽምቅ ተዋጊ…

Read More

የምክር ቤቱ አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እስካሁን ያቀረቧቸው ዋና ዋና ጥያቄዎች

ከአሸባሪው ኦነግ ሸኔ ጋር የተደረገው ንግግር ያልተሳካው በምን ምክንያት ነው፤ በአማራ ክልል የተወሰደው ህግ የማስከበር እርምጃ በምን ደረጃ ላይ ይገኛል፤ የአማራ ክልል ነባራዊ ሁኔታ ከውጭ ሃይሎች ጣልቃ ገብነት ምን ያህል የጸዳ ነው፤ መንግስት የተዛቡ ችግሮችን ለማረምና አሰባሳቢ ትርክት ለመገንባት እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን የተመለከተ ማብራሪያ ቢሰጥ፤ በመንግስትና በፓርቲ ውስጥ ያሉ ዋልታ ረገጥ አስተሳሰቦች ያላቸው ተዋንያንን ለማስተካከል…

Read More

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 14ኛ መደበኛ ስብሰባ መካሄድ ጀመረ!

የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 14ኛ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ማካሄድ ጀምሯል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በምክር ቤት ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። ምክር ቤቱ፤ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 55 (17) በተቀመጠውና በምክር ቤቱ የአሠራር እና የአባላት ስነምግባር ደንብ ቁጥር 6/2008 መሠረት፤ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)…

Read More

በጋራ ለሠሩ መሪዎች ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ምሥጋና አቀረቡ::

የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በባሕር ዳር ከተማ ከእርሳቸው ጋር ተገኝተው ሕዝባዊ ውይይቱን ለመሩት የሶማሌ ክልል ርእሰ መሥተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ እና ለመንግሥት ተጠሪ ሚኒስትሩ ተሥፋዬ በልጂጌ የክብር ካባ አልብሰዋል። ርእሰ መስተዳድር አረጋ “ወንድሜ ሙስጦፌ በሶማሌ ክልል የሚኖሩ ሁሉም ብሔር ብሔረሰቦች እኩል ተከብረው እና ደኅንነታቸው ተጠብቆ እንዲሠሩ እና እንዲኖሩ ያስቻሉ መሪ ናቸው” ሲሉ ተናግረዋል። አማራ…

Read More

በቦስተን የኒው ባላንስ የቤት ውስጥ ውድድር ጉዳፍ ፀጋይና ለሜቻ ግርማ አሸነፉ::

በቦስተን የኒው ባላንስ የዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ውድድር ጉዳፍ ፀጋይ እና ለሜቻ ግርማ ውድድሩን በበላይነት አጠናቅቀዋል፡፡ በ1 ሺህ 500 ሜትር የተወዳደረችው ጉዳፍ ፀጋይ ርቀቱን በ3 ደቂቃ 58 ሰከንድ ከ11 ማይክሮ ሰከንድ በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ ቀዳሚ ሆናለች፡፡ በዚሁ ርቀት የ18 ዓመቷ አትሌት ብርቄ ሀየሎም 3 ደቂቃ 58 ሰከንድ ከ43 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት 2ኛ ደረጃን ይዛለች፡፡ ወጣቷ…

Read More

የክልሉ ምክር ቤት ጉባዔ ከጥር 30/2016 ጀምሮ ሊካሄድ ነዉ::

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ምክርቤት 6ኛ ዙር 3ኛ የስራ ዘመን 5ኛ መደበኛ ጉባዔ ከፊታችን ጥር 30/2016 እስከ የካቲት 1/2016 ዓ/ም በታርጫ ከተማ እንደሚካሄድ አስታወቀ። ጉባኤውን አስመልክቶ መግለጫ የሰጡት የክልሉ ምክርቤት ዋና አፈ ጉባዔ የተከበሩ አቶ ወንድሙ ኩርታ ለጉባኤው አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸውን ተናግረዋል ። በዚህም ለጉባኤው ተሳታፊዎች ጥሪ መተላለፉን አፈጉባዔ ወንድሙ ኩርታ…

Read More