በአሳታፊ አነስተኛ መስኖ ልማት ፕሮግራም የአርሶአደሩን ኑሮ ለማሻሻል በተሰራው ስራ አዎንታዊ ውጤት ተመዝግቧል። አቶ ማስረሻ በላቸው
በክልሉ ሁለት ወረዳዎች ሲተገበር የነበረው የአሳታፊ አነስተኛ መስኖ ልማት ፕሮግራም ምዕራፍ ሁለት በእንግሊዝኛው (PASSDIP-II) መዝጊያ መርሀግብር የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ሀላፊ አቶ ማስረሻ በላቸውና ለሌሎች የባለድርሻ አካላት በተገኙበት በቦንጋ ከተማ ተካሂዷል። ፕሮግራሙ ከ7 ዓመታት በፊት በዳውሮ ዞን ሎማ ቦሳ እና ጌና ወረዳ ሁለት ቀበሌያትን በማቀፍ በአነስተኛ የውሃ መስኖ አውታር ግንባታ የአርሶአደሩን ኑሮ በማሻሻል…
