ዘንድሮ ከ50 ዓመታት በኃላ ለ2ተኛ ጊዜ የሚከበረው የሸኮ ብሄር ዘመን መለወጫ እና ምስጋና በዓል “ቲከሻ ቤንጊ”የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ተገመገመ

ዘንድሮ ከ50 ዓመታት በኃላ ለ2ተኛ ጊዜ የሚከበረው የሸኮ ብሄር ዘመን መለወጫ እና ምስጋና በዓል “ቲከሻ ቤንጊ” በድምቀት ለማክበር በትኩረት እየተሰራ ይገኛል። በዓሉ በድምቀት እንዲከበር እንዲሁም ለትውልድ ለማስተላለፍ ሶስቱ ወረዳዎችና ሶስቱ ከተማ አስተዳደሮች በቅንጅት እና ትብብር መስራት ከጀመሩ ሰንብቷል። ለዚሁም ተግባር ስኬታማነት የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ሪፖርት ባለድርሻ አካላት በተገኙት ተገምግሟል ። በመድረኩ ክቡር አፈ ጉባኤ ወንድሙ…

Read More

አቶ አደም ፋራህ በአዳማ ከተማ አስተዳደር የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ ስርዓትን ጎበኙ

በምክትል ጠቅላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ በአዳማ ከተማ አስተዳደር የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ ስርዓትን ጎበኙ። አቶ አደም ፋራህ፣ በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በአዳማ ከተማ አስተዳደር በሁሉም የከተማ አስተዳደሩ ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶችን በተናበበና በተቀናጀ መልኩ በአንድ ማዕከል ለመስጠት የተቋቋመውና “ጋዲሳ ኦዳ” የሚል ስያሜ የተሰጠውን…

Read More

በካፋ ዞን ሳይለም ወረዳ እየተከናወኑ ያሉ የተለያዩ የልማት ሥራዎች በዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ በተመራው የዞን ከፍተኛ አመራሮች ልዑክ እየጎበኙ ነዉ።

በወረዳ ከኤምርኪ አጋሮ ቀበሌ ጀምሮ የተለያዩ የመንገድ መሠረተ ልማቶችና የግብርና ልማት ተግባራት በካፋ ዞን ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተጎብኝቷል። ከኤምርኪ ወደ አጋሮ ቀበሌ የሚያደርስ በህዝብ ተሳትፎ እየተሰራ የሚገኝ የአፈር ሥራ ያለቀለት የ7 ኪ/ሜ መንገድ ከፈታ ሥራ የጉብኝቱ አካል ሆኗል። በተጨማሪ በቴክኖሎጂ ተጠቅሞ ያመረቱት የአርሶ አደር ስንዴ ማሳ እንድሁም የኤምርኪ አርሶ አደር ማሰልጠኛ ውስጥ የሚከናወኑ የተለያዩ የግብርና…

Read More

የከተሞች ፈርጅ ለውጥ ለከተሞች እድገትና ለአገለግሎት አሰጣጥ መሻሻል ጉልህ ሚና እንዳለው ተገለጸ

የክልሉ መንግስት ለህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ ለመሰጠት ቅድሚያ ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝም ተብራርቷል። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በዳውሮ ዞን የታርጫ ከተማ ከፈርጅ ሶስት ወደ ፈርጅ ሁለት ያደገበት ይፋዊ የስራ ማስጀመሪያ መርሃግብር ተካሂዷል። በመርሃግብሩ የተገኙ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ሀላፊ ኢንጂነር የማታለም ቸኮል የክልሉ መንግስት ለህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር…

Read More

ከ742 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ በቦንጋ ከተማ ግንባታ እየተከናወነ የሚገኘው የኢትዮጵያ ግብርና ኮርፖሬሽን የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት መስጫ ማዕከል ግንባታ 98 ከመቶ መድረሱ ተገለጸ።

ግብርናን ለማዘመን መንግሥት ከፍተኛ ትኩረት አድርጎ እየሰራ ይገኛል። ከነዚህ የመንግሥት ጥረቶች አንዱ የግብርና ግብዓቶችን በተደራጀ እና በተቀናጀ መልኩ ለአምራቾች ተደራሽ የማድረግ ተግባር ሲሆን በደቡብ ምዕራብ ቀጠና ይህንኑን ተግባር የሚያሳልጠው የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት መስጫ ማዕከል ግንባታ ፕሮጀክት ግንባታ በ2014 በጀት ዓመት ማገባደጃ ወደ ግንባታ መግባቱን ነው የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ አማካሪ አቶ ካሳሁን…

Read More

በሕገ-ወጥ ድርጊት በሚሳተፉ አካላት ላይ የሚወሰደው ርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል፦አገልግሎቱ

በሕገ-ወጥ ድርጊት በሚሳተፉ አካላት ላይ የሚወሰደው ርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ፡፡ አገልግሎቱ በሰጠው መግለጫ÷ የፋይናንስ ወንጀሎች በሀገር ላይ የሚያደርሱት ጉዳት ዘርፈ ብዙ እና ከፍተኛ መሆኑን አስረድቷል፡፡ በመሆኑ ኢትዮጵያ ወንጀሎቹን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የተለያዩ ህጎችን አውጥታ በመተግባር እንደምትገኝም አስገንዝቧል፡፡ ለአብነትም በወንጀል ድርጊት የተገኘ ገንዘብ ወይም ንብረት ህጋዊ አስመስሎ የማቅረብና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣው…

Read More

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የጥምቀት በዓል እየተከበረ ነው

በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የጥምቀት በዓል በአዲስ አበባ ልደታ ማሪያም ካቶሊክ ካቴድራል ቤተክርስቲያን እየተከበረ ይገኛል። በበዓሉም የሃይማኖት አባቶች፣ የእምነቱ ተከታዮች ምዕምናንና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል። በዓሉ በቅዳሴ፣ በፀሎት፣ በዝማሬ፣ በምስጋና እና በሌሎች ሃይማኖታዊ ሥነ-ሥርዓቶች በድምቀት እየተከበረ መሆኑን ኢዜአ ዘግቧል። በዓሉ በመላው ሀገሪቱ ባሉ የካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ተከብሮ እንደሚውልም ተገልጿል ሲል ደሬቴድ ዘግቧል።

Read More

በጎንደር የተመዘገቡ ስኬቶችን ቀጣይነት ለማረጋገጥ ሰላምን ማጽናት ይገባል – ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ

በጎንደር የተመዘገቡ ስኬቶችን ቀጣይነት ለማረጋገጥ ሰላምን ማጽናት እንደሚገባ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ገለጹ። ጥምቀት በጎንደር ፋሲለደስ ባህረ ጥምቀት የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የኃይማኖት አባቶች፣ የውጭ ሀገር ጎብኚዎች እና በርካታ ምዕመናን በታደሙበት በድምቀት እየተከበረ ይገኛል። ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት የጎንደር ከተማ የሚመጥናት የእድገት ማማ ላይ መውጣት የምትችልበት ዘመን ነው። የጎንደር ከተማ በፈጣን…

Read More